በትግራይ ክልል መቀመጫቸውን ያደረጉ ሦስቱ ክለቦች የጋራ ውይይት ሊያደርጉ ነው
ዘንድሮ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ላይ ሳይሳተፉ የቀሩት በትግራይ ክልል የሚገኙት ሦስቱ ክለቦች በአመራሮቻቸው በኩል ስብሰባ ሊቀመጡ ነው።
መቐለ ሰባ እንደርታ፣ ወልዋሎ እና ሱሑል ሽረ በወቅታዊው ሀገራዊ ሁኔታ ምክንያት በዘንድሮው የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተሳታፊ አለመሆናቸውን ተከትሎ ሊጉ በአስራ ሦስት ክለቦች መካከል መካሄዱ ይታወቃል። በቀጣይ ዓመት ዳግም ወደ ውድድሩ ይመለሳሉ ወይስ ሊግ ካምፓኒው ባወጣው የመፍትሄ ሀሳብ መሠረት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ተደርገው ለከርሞ በአስራ ስድስት ክለቦች ይቀጥላል የሚለው የብዙ የስፖርት ቤተሰቦች ጥያቄ ሆኗል።
በቅርቡ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መቀመጫቸውን ትግራይ ካደረጉ ሦስቱ ክለቦች ጋር መገናኘት መጀመሩን መዘገባችን ይታወቃል። አሁን በደረሰን መረጃ መሠረት ደግሞ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የትግራይ ክልል ስፖርት ኮሚሽንና የትግራይ ክልል እግርኳስ ፌዴሬሽን እንዲሁም የሦስቱ ክለቦች አመራሮች በተገኙበት ስብሰባ ሊቀመጡ እንደሆነ ሰምተናል። በውይይታቸውም በዋናነት በቀጣይ ዓመት ወደ ውድድር የሚመለሱበትን መንገድ እንዴት እንደሚሆን ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህ ጉዳይ የሚኖሩ አዳዲስ ነገሮችን እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን ከወዲሁ እንጠቁማለን።
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...