ዐፄዎች የተጨማሪ ተጫዋች ውል አድሰዋል

ኪሩቤል ኃይሉ በፋሲል ከነማ ቆይታውን አራዝሟል።

እስካሁን ሦስት አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ የተቀላቀሉት ፋሲሎች ረፋድ ላይ የተከላካዩ ዳንኤል ዘመዴን ውል ለተጨማሪ ኣመት እንዳራዘሙ ይታወቃል፡ አሁን ደግሞ የኪሩቤል ኃይሉን ውል አራዝመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ፍሬ የሆነው የተከላካይ አማካይ ሥፍራ ተጫዋቹ ዘንድሮ በክለቡ ብዙም የመሰለፍ ዕድል እያገኘ ባይሆንም ክለቡ ለተጨማሪ ዓመት እንዲቆይለት ውሉን አድሷል፡፡