ባህር ዳር ከተማ አራተኛ ተጫዋች አስፈርሟል
በ2014 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተጠናክሮ ለመቅረብ ዝውውሮች ላይ ጠንክሮ እየሰራ የሚገኘው ባህር ዳር ከተማ አራተኛ ተጫዋች አስፈርሟል።
አሠልጣኝ አብርሃም መብራቱን ከቀጠሩ በኋላ ፉዐድ ፈረጃ፣ መሳይ አገኘሁ እና ተመስገን ደረሰን የግላቸው ያደረጉት ባህር ዳር ከተማዎች ከደቂቃዎች በፊት በሁለት ዓመት ውል አለልኝ አዘነን ወደ ስብስባቸው ቀላቅለዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የእግር ኳስ ህይወቱን በ2008 የጀመረው እና በክለቡም እስከ 2011 ድረስ የቆየው ቁመተ መለሎው ተጫዋች ከ2012 እስከ ተጠናቀቀው የውድድር ድረስ ደግሞ በሀዋሳ መለያ በመጫወት አሳልፏል፡፡ በ2012 በቅጣት ለአንድ ዓመት ከሜዳ ርቆ በ2013 አጋማሽ ወደ ሜዳ የተመለሰው አማካዩ ወደ ጣና ሞገዶቹ ቤት በሁለት ዓመት ውል አምርቷል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...