
ጅማ አባጅፋር ተጨማሪ ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል
ከሰዓታት በፊት እያሱ ለገሠን የግሉ ያደረገው ጅማ አባጅፋር አሁን ደግሞ የሁለት ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቋል።
ቡድኑን የተቀላቀለው የመጀመሪያው ተጫዋች ተስፋዬ መላኩ ነው። የቀድሞው የወላይታ ድቻ፣ ኤሌክትሪክ እና ሀዋሳ ከተማ ሁለገብ ተጫዋች የሆነው ተስፋዬ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወራት በወልቂጤ ከተማ ቆይታ ያረገ ሲሆን አሁን ደግሞ በ2011 ተጫውቶ ወዳሳለፈበት ጅማ አባ ጅፋር አምርቷል።
ሁለተኛው ተጫዋች ደግሞ የግብ ዘቡ ዩሐንስ በዛብህ ነው። የንግድ ባንክ፣ ሀዋሳ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ቡና እና ኤሌክትሪክ ግብ ጠባቂ የተጠናቀቀውን የውድድር ዓመት በወልቂጤ ከተማ ማሳለፉ ይታወቃል። አሁን ደግሞ እንደ ቡድን አጋሩ ተስፋዬ ሁሉ መዳረሻው ጅማ ሆኗል።
በኤሌክትሪክ እና ወልቂጤ የቡድን አጋር የነበሩት ሁለቱ ተጫዋቾች ለሦስተኛ ጊዜ በአንድ ቡድን የሚገናኙ ይሆናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች ከመቋረጡ አስቀድሞ የሚደረጉትን የነገ ጨዋታዎች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ሲዳማ ቡና የነገው የጨዋታ ቀን...
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
ሪፖርት | ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊስን ያለመሸነፍ ጉዞ ገቷል
እጅግ ተጠባቂ በነበረው የዕለቱ የመጨረሻ ጨዋታ ፋሲል ከነማ በኦኪኪ አፎላቢ ጎል ቅዱስ ጊዮርጊስን 1-0 በማሸነፍ የነጥብ ልዩነቱን ወደ አምስት ቀንሷል።...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 3-0 ሰበታ ከተማ
ለሰባ አራት ደቂቃዎች በጎዶሎ ተጫዋቾች የተጫወተው አዳማ ከተማ ሶስት ነጥብ ካገኘበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ አሰልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ...