
ወደ ሴቶች ሁለተኛ ዲቪዚዮን ያደጉ ክለቦች ሙሉ በሙሉ ተለይተው ታውቀዋል
በሁለት ምድብ ተከፍሎ በአስር ክለቦች መካከል በሀዋሳ ሲደረግ የነበረው የክልል ክለቦች ሻምፒዮና የምድብ ጨዋታዎች ተጠናቀዋል፡፡
ወደ ኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዲቪዚዮን የሚያድጉ ክለቦችን ለመለየት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተደረገ ያለው ይህ ውድድር ከቀናቶች በፊት አላፊ ስድስት ቡድኖች ተለይተው የታወቁ ሲሆን የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ትላንት በሀዋሳ ግብርና ኮሌጅ ተከናውነው ቀሪዎቹ ሁለት ቡድኖቹም ታውቀዋል፡፡
ወላይታ ዞን 3-0 ሰበታ ከተማ
ሱሉልታ ከተማ 1-2 ፔንዳ ክለብ
ሀላባ ዞን 10-1 ምስራቅ ክፍለከተማ
አለታ ወንዶ 0-3 አሰላ ከተማ
በተጠቀሱት ጨዋታዎች እና ቀደም ብለው በተመዘገቡ ውጤቶች መሠረት ከምድብ ሀ አራዳ ክፍለከተማ፣ ሀላባ ዞን፣ ወላይታ ዞን እና ሰበታ ከተማ፤ ከምድብ ለ ሱሉልታ ከተማ፣ ከንባታ ዞን፣ አሰላ ከተማ እና ፔንዳ ክለብ ማለፋቸውን ሲያረጋግጡ ከሲዳማ ክልል የተወዳደሩት ምስራቅ ክፍለከተማ እና አለታ ቤዛ ውሀ ወደ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ሳይገቡ ከምድባቸው ወድቀዋል፡፡
የፊታችን ማክሰኞ ነሐሴ 5 የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ሱሉልታ ከተማ ከ ሀላባ ዞን 8፡00
አራዳ ክፍለከተማ ከ ከምባታ ዞን 10፡00
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...