
አሠልጣኝ ካሣዬ እና ኢትዮጵያ ቡና ከስምምነት የደረሱ ይመስላል
ከተጫዋቾቹ ጋር ወደ ቢሾፍቱ ሳይጓዝ የቀረው አሠልጣኝ ካሣዬ ክለቡ ያስቀመጠውን አቅጣጫ በጊዜያዊነት መቀበሉ ታውቋል።
በተጠናቀቀው የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያገባደደው ኢትዮጵያ ቡና ከፊቱ ላለበት የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ዝግጅቱን ለማድረግ በሳምንቱ መጀመሪያ ቀናት (ማክሰኞ) ወደ ቢሾፍቱ ማምራቱ ይታወቃል። የቡድኑ ተጫዋቾች እና አንደኛው ምክትል አሠልጣኝ ገብረኪዳን ነጋሽ በታሰበው ቀን ወደ ቢሾፍቱ ቢያመሩም ዋና አሠልጣኙ ካሣዬ አራጌ የምክትል አሠልጣኙ ዘላለም ፀጋዬ ውል አለመታደስ አስከፍቶት ወደ ስፍራው ሳያቀና ቀርቶ ነበር። ይህንን ተከትሎም አሠልጣኝ ካሣዬ ክለቡ የረዳቱን ውል እንዲያድስለት ደብዳቤ አስገብቶ ምላሽ ሲጠባበቅ እንደነበር ይታወቃል።
የአሠልጣኙን ጥያቄ ከሁለት ቀን በፊት (ሀሙስ ምሽት) ሲመለከት የነበረው የክለቡ የሥራ አመራር ቦርድም ሥራ እንዳይበደል አሠልጣኙ ቡድኑን እያዘጋጀ ጥያቄውን እንዲያቀርብ አቅጣጫ አስቀምጦ ነበር። ይህ ክለቡ የሰጠውን ሀሳብ ተቀብሎም አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ በዛሬው ዕለት ቡድኑ ወዳረፈበት ቢሾፍቱ ከተማ ማቅናት ከተጫዋቾቹ ጋር ትውውቅ ሰላምታ እንደተለዋወጠ እንዳደረገ ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሰልጣኝ ካሣዬ ወደ ስፍራው ያቅና እንጂ ምክትል አሰልጣኙ በቀናት ውስጥ ውሉ ታድሶለት ከቡድኑ ጋር የማይቀላቀል ከሆነ ዳግመኛ ጉዳዩ ወደ ሌላ ምዕራፍ እንዳይሻገር ተሰግቷል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...