
በሴቶች ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ለፍፃሜ የደረሱ ክለቦች ተለይተዋል
በሀዋሳ እየተደረገ ያለውን የኢትዮጵያ ሴቶች ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የፊታችን ቅዳሜ በሚደረጉ የደረጃ እና የፍጻሜ ጨዋታዎች ይጠናቀቃል፡፡
በሀዋሳ ከተማ ከሐምሌ 19 ጀምሮ በአስር ክለቦች መካከል በሁለት ምድቦች ተከፍሎ ሲደረግ የነበረው የኢትዮጵያ ሴቶች ክልል ክለቦች ሻምፒዮና አስቀድሞ በተደረጉ ጨዋታዎች ስምንት ክለቦች ወደ 2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዲቪዚዮን ማደጋቸውን ያረጋገጡ ሲሆን በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ግብርና ኮሌጅ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለዋንጫ ፍፃሜ ያለፉ ሁለት ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል፡፡
ቀደም ብሎ 3፡00 ሲል በተደረገው ጨዋታ የአዲስ አበባ ከተማው አራዳ ክፍለ ከተማ ከምባታ ዞንን 1ለ0 ሲረታ የኦሮሚያ ክልሉ ሱሉልታ ከተማ ሀላባ ዞንን 4 ለ3 በማሸነፍ ወደ ፍፃሜው አልፈዋል፡፡
ውድድሩ የፊታችን ቅዳሜ ነሀሴ 8 ረፋድ በሚደረጉ የደረጃ እና የፍፃሜ ጨዋታዎች ይጠናቀቃል፡፡
ለደረጃ – ከንባታ ዞን ከ ሀላባ ዞን 3፡00
ለዋንጫ – አራዳ ክፍለከተማ ከ ሱሉልታ ከተማ 5፡00
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ንግድ ባንክ በጎል ተንበሽብሾ ሲያሸንፍ አርባምንጭ እና ባህር ዳር ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ሁለት ቀሪ ጨዋታዎች ዛሬ ሲከወኑ መሪው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በግማሽ ደርዘን ጎል ድሬዳዋን ሲያሸንፍ...
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...