
አዲሱ የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ቅዳሜ አዲስ አበባ ይገባሉ
ከሳምንታት በፊት የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ሆነው የተሾሙት ሰርቢያዊ ቅዳሜ አዲስ አበባ እንደሚገቡ ይፋ ተደርጓል።
የ64 ዓመቱ ሰርቢያዊ ዝላትኮ ክራምፖቲች በዋና አሰልጣኝነት የሾሙት ቅዱስ ጊዮርጊሶች አዲሱ አሰልጣኝ ከሰርቢያዊው ምክትላቸው ኒኮላ ኮሮሊጃ ጋር በመሆን በመጪው ቅዳሜ አዲስ አበባ እንደሚገቡ ያስታወቀ ሲሆን በተመሳሳይ ዕለት የዋናው ቡድን አባላት በዘሪሁን ሸንገታ እየተመሩ ለቅድመ ውድድር ዝግጅት ቢሾፍቱ ወደሚገኘው የክብር ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ እንደሚከትሙም ክለቡ በይፋዊ የሬዲዮ ፕሮግራም ይፋ አድርጓል።
በቀጣዩ ቀናት አዳዲሶቹ አሰልጣኞች ከክለቡ አመራሮች እና የቡድን አባላት ጋር ትውውቅ እንደሚያደርጉ ሲጠበቅ በመጪው ሰኞም አሰልጣኙ በክለቡ ፅህፈት ቤት በሚደረግ ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ አሰልጣኙን በይፋ እንደሚያስተዋውቁ ተገልጿል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...