
የአማካይ መስመር ተጫዋቹ ከዋልያው ስብስብ ውጪ ሆኗል
ከሦስት ቀናት በፊት በልምምድ ላይ ጉዳት ያጋጠመው የአማካይ መስመር ተጫዋች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ውጪ ሆኗል።
በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለማለፍ ከጋና እና ዚምባቡዌ ጋር ከያዝነው ወር መጨረሻ ጀምሮ ጨዋታ ያደርጋል። ከሳምንት በፊት ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ልምምድ የጀመረው ቡድኑም ማክሰኞ ወደ አዳማ በማቅናት ልምምድ እንደጀመረ ይታወቃል።
ሶከር ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኑ የረቡዕ አመሻሽ ልምምዱን ሲሰራ በስፍራው ተገኝታ እንደዘገበችውም የመሐል ሜዳ ተጫዋቹ ሀብታሙ ተከስተ ከሌላ ተጫዋች ጋር ጉዳት አስተናግዶ ከሜዳ ወጥቶ ነበር። ድረ-ገፃችን የተጫዋቹን የጉዳት ምንነት እና መጠን ለማጣራት ያደረገችው ጥረት ለአሁን ባይሳካም ተጫዋቹ ባጋጠመው ጉዳት ከስብስቡ ሙሉ ለሙሉ ውጪ እንደሆነ ተረድታለች።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...