
ሰበታ ከተማ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ቀጥሯል
.
በአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው መሪነት በሀዋሳ ከተማ የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን እየሰራ የሚገኘው ሰበታ ከተማ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ቀጥሯል፡፡
ለ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን በሀዋሳ ከተማ እየሰራ የሚገኘው ሰበታ ከተማ አዳዲስ እና ነባር ተጫዋቾቹን በመያዝ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ከሳምንታት በፊት ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማሪያምን በረዳት አሰልጣኝነት የቀጠረው ክለቡ አሁን ደግሞ ሦስተኛ ወይንም የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ በማድረግ ኢያሱ ደስታን ምርጫው አድርጓል፡፡
የቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወላይታ ድቻ ግብ ጠባቂ የነበረው ኢያሱ ኳስን ካቆመ በኃላ ተጫውቶ ባሳለፈበት ወላይታ ድቻ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ በመሆን ጅምሩን ያደረገ ሲሆን ከክለቡም ጋር ከተለያየ በኋላም የተጠናቀቀውን የውድድር ዓመት ከሀድያ ሆሳዕና ጋር አሳልፏል፡፡ ከግብ ጠባቂ አሰልጣኝነት ሚናው በተጨማሪም ክለቡ ከተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ጋር ውዝግብ በገባበት ወቅት አንድ ጨዋታ ላይ (ከሀዋሳ ከተማ) ቡድኑን የመራ ሲሆን ድህረ ጨዋታ አስተያየት ሲሰጥ መስተዋሉም የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነበር። አሰልጣኝ ኢያሱ ውሉ ከክለቡ ጋር መጠናቀቁን ተከትሎ ማረፊያውን ሰበታ ከተማ አድርጓል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ | 24ኛ ሳምንት ምርጥ 11
እንደ ሁልጊዜው ባሳለፍነው ሳምንት በተደረጉ ጨዋታዎች ላይ ጎልተው የወጡ ተጫዋቾችን ያካተተ ቡድን ሰርተናል። አሰላለፍ (4-3-2-1) ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ -...
ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል
የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል። በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ...
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል
10:00 ላይ ከናይጄሪያ አቻው ጋር ወሳኝ ጨዋታ የሚጠብቀው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰላለፍ ታውቋል። በሕንድ ለሚደረገው የሴቶች...
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 21ኛ ሳምንት ዓበይት ጉዳዮች (፫) – አሰልጣኞች ትኩረት
በሦስተኛው የሳምንቱ የዓበይት ጉዳይ ፅሁፋችን አሰልጣኞች ላይ ያተኮሩ ሀሳቦች ተዳሰውበታል። 👉 ፋሲል ተካልኝ እና አዳማ ተለያይተዋል በክረምቱ አዳማ ከተማን የተረከበው...
በሦስት ዳኞች ላይ ውሳኔ ተላልፏል
በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ ዳኞች ከፕሪምየር ሊጉ ውድድር ተሸኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታ...