
አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ በሀዋሳ ከተማ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች የኳስ ስጦታ አበርክቷል
አዲሱ የሀዋሳ ከተማ ዋና አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ በከተማዋ ለሚገኙ አምስት የታዳጊ ፕሮጀክቶች በርከት ያሉ የኳስ ስጦታዎችን በዛሬው ዕለት አበርክቷል፡፡
የቀድሞው የሲዳማ ቡና እና አዳማ ከተማ እንዲሁም በቅርቡ የሀዋሳ ከተማ ዋና አሰልጣኝ በመሆን በሁለት ዓመት ውል የተሾሙት አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ በሀዋሳ ከተማ በታዳጊ እግርኳስ ላይ ሲለፉ ለነበሩ አምስት ፕሮጀክቶች በርከት ያሉ ኳሶችን በስጦታ መልክ አበርክተዋል፡፡ በሀዋሳ ከተማ ሲደረግ ቆይቶ ከቀናቶች በፊት በተጠናቀቀው የሴንትራል ዋንጫ የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው የነበሩት አሰልጣኙ በታዳጊ ተጫዋቾች ላይ ሲለፉ የነበሩ ፕሮጀክቶችን ከታዘቡ በኋላ በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ጠርተው ከ13 ዓመት በታች ሁለት ከ15 ዓመት በታች ሁለት እና ከ17 ዓመት በታች አንድ በድምሩ ለአምስት ፕሮጀክቶች በርከት ያሉ የኳስ ስጦታዎችን አበርክተዋል፡፡
አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ ለተጫዋቾቹ ካበረከቱት ስጦታ በኋላ ለሶከር ኢትዮጵያ እንደተናገሩት “ጊዜው ይህን ያስገድዳል ሁሉም ለታዳጊ ቡድኖች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል። እኔም ይህን መነሻ በማድረግ አበርክቻለሁ። ሀዋሳ ውስጥ ያሉ ፕሮጀክቶችን ተመልክቻለሁ። በዚህም በጣም ደስተኛ ነኝ። ሁሌም ከቡድኖቹ ጎን በመቆም ታዳጊዎች እንዲፈሩ የሚቻለኝን ሁሉ ለማድረግ ተዘጋጅቻለሁ። በቀጣይም ፕሮጀክቶቹ ከበረቱ እና ከጠነከሩ የትጥቅ ድጋፍን በተጨማሪነት አደርጋለሁ።” ሲሉ የተናገሩ ሲሆን አሰልጣኙ በቀጣዮቹ ዓመታት በታዳጊ ተጫዋቾች ላይ ትኩረት ሰጥተው በክለብ ደረጃ በደንብ ለመስራት መነሳሳት እንደፈጠረላቸውም ጠቁመዋል፡፡ ስጦታ የተበረከተላቸው የፕሮጀክቶቹ አሰልጣኞችም አሰልጣኙ ላደረጉላቸው መልካም ተግባር ምስጋና አቅርበው ሌሎች የሀገሪቱ አሰልጣኞች ተመሳሳይ ድጋፍን እና ሙያዊ እገዛለን በያሉበት ሆነው ቢያደርጉ የሀገራችንን እግር ኳስ ከፍ ማድረግ ይቻላል ሲሉ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...