
ሀዲያ ሆሳዕና በፍርድ ቤት ተጨማሪ እግድ ተላለፈበት
ከተጫዋቾች ዝውውር ጋር በተያያዘ ከዚህ ቀደም በአራት ተጫዋቾች የፍርድ ቤት ዕግድ የተላለፈበት ሀድያ ሆሳዕና አሁን በአንድ ተጫዋች ክስ ምክንያት እግድ መተላለፉ ታውቋል።
የ2013 የውድድር ዘመን ለሀዲያ ሆሳዕና ሲጫወት የቆየው አዲስ ህንፃ ከክለቡ ጋር በተስማማሁት መሠረት በቼክ የተቀበልኩት አምስት መቶ ሰባ ስድስት ሺህ ብር አልተከፈለኝም በማለት በአቶ ብርሐኑ በጋሻው የሕግ አማካሪ ጠበቃ እና የአግር ኳስ ስፖርትኞች ሕጋዊ ወኪል አማካኝነት ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በማምራት ሲከታተል ቆይቷል።
በመጨረሻም ልደታ 5ኛ ምድብ የፍ/ብሔር ችሎት በሀድያ ሆሳዕና ላይ ከሊግ ካምፓኒው ከሚያገኘው ድርሻ አምስት መቶ ሰባ ስድስት ሺህ ብር አግዶ እንዲቆይ ውሳኔ አሳልፏል።
ይህን እግድ ተከትሎ ሀዲያ ሆሳዕና ከሊግ ካምፓኒው ከሚያገኘው የገቢ ክፍፍል ላይ በአጠቃላይ 2.57 ሚልዮን ብር ታግዶበት የሚቆይ ይሆናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...