
ኢትዮጵያዊያን ዳኞች የካፍ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫን ይመራሉ
አራት ኢትዮጵያዊያን ዳኞች የኮንፌዴሬሽን ጨዋታን ለመምራት አመሻሽ ወደ ወደ ዲሞክራቲክ ኮንጎዋ ዋና ከተማ ኪንሻሳ ያቀናሉ፡፡
የካፍ የ2021 የኮንፌዴሬሽን ጨዋታዎች በያዝነው ሳምንት መደረጋቸውን ሲቀጥሉ ከቻምፒዮንስ ሊጉ የማጣሪያ ጨዋታዎች ውጪ የነበሩት የዲሞክራቲክ ኮንጎው ኤ ኤስ ማኒዬማ ዩኒየን ከግብፁ ፒራሚድ ክለብ ጋር የኮንፌዴሬሽን የፕሌይ ኦፍ መርሀ-ግብራቸውን ኪንሻሳ በሚገኘው ስታድ ዴ ማርቲርስ በተባለው አርቴፊሻል ሜዳ ላይ የፊታችን ዕሁድ ምሽት 12፡00 ላይ ይጫወታሉ፡፡
ይህንን ጨዋታ አራት ኢትዮጵያዊያን የሚመሩት ሲሆን ወደ ስፍራውም ዛሬ ምሽት ያመራሉ፡፡ በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ እየዳኙ የሚገኙት በላይ ታደሰ በመሐል ዳኝነት፣ ክንዴ ሙሴ እና ትግል ግዛው በረዳት ዳኝነት የተመደቡ ሲሆን አራተኛ ዳኛ በመሆን ደግሞ ለሚ ንጉሤ ወደ ስፍራው እንደሚያቀኑ ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች፡፡ ሩዋንዳዊው አሌክሲስ ረዳምፕተስ ደግሞ የጨዋታ ታዛቢ ናቸው፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...