የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር እጣ ወጥቷል

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ደንብ ውይይት ካደረገ በኋላ በቅድሚያ የኢትዮጵያ ሴቶች ሊግ ውድድርን እጣ በአሁኑ ሰዓት አውጥቷል። በሊጉ ተሳታፊ የሚሆኑ 13 ክለቦች ተወካዮች ባሉበት በወጣው እጣ መሰረትም በቅድሚያ ሀዋሳ ከተማ የሚደረገው የውድድሩ መርሐ-ግብር ወጥቷል።

የመጀመርያ ሳምንት ጨዋታዎች

ቦሌ ክ/ከተማ ከ መከላከያ
አዳማ ከተማ ከ አቃቂ ቃ/ክ/ከተማ
ሀዋሳ ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ
አዲስ አበባ ከተማ ከ ባህር ዳር ከተማ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ አርባምንጭ ከተማ

* የመጀመሪያ ሳምንት አራፊ ቡድን ጌዲዮ ዲላ