
የአሰልጣኝ እስማኤል አቡበከር እና የቡድን መሪው የፍርድ ቤት ውሎ…
በሁለቱ አካላት ዙርያ የተፈጠረው ውዝግብ ወደ መደበኛ ፍርድቤት አምርቶ ጉዳያቸው በዛሬው ዕለት በችሎት ታይቷል።
ከዚህ ቀደም በነበረው ተደጋጋሚ ዘገባችን የአዲስ አበባ የቀድሞ አሰልጣኝ እስማኤል አበቡበከር እና የቡድን መሪው አቶ ሲሳይ ተረፈ መካከል የተፈጠረ ውዝግብ ወደ ኃይል አምርቶ ክለቡ የቀረበለትን ሪፖርት ከመረመረ መኃላ የተለያዩ ውሳኔዎችን ማሳለፉ ይታወቃል። ይህ በዚህ ያላቆመው የሁለቱ አካላት ጉዳይ ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት አምርቶ ክስ መመስረቱም ይታወሳል።
በዚህም መሠረት የመጀመርያ ቀጠሯቸውን አክብረው በዛሬው ዕለት በሲዳማ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍ/ችሎት በመገኘት ጉዳያቸው የታየ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ተለዋጭ ቀጠሮ ለህዳር 24 በመስጠት ሸኝቷቸዋል። እየወጡ ባሉ ዘገባዎች ከሆነ ይህ ጉዳይ እየከረረ በመሄድ ሌሎች አዳዲስ ክሶች በሁለቱም ወገን ሊከፈት እንደሚችል ሰምተናል።
በትናትንናው ምሸት አዲስ አበባ ከተማ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ አሰልጣኝ እስማኤል አቡበከርም ሆነ የቡድን መሪው አቶ ሲሳይ ተረፈ በክቡር ትሪቡን በመገኘት ጨዋታውን ሲከታተሉ እንደነበረ ታዝበናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...