
ኢትዮጵያዊያን እንስት ዳኞች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታን ይመራሉ
አራት ኢትዮጵያዊያን ሴት ዳኞች የዓለም ከ20 ዓመት በታች ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታን ለመምራት ወደ ዩጋንዳ ያቀናሉ፡፡
ኮስታሪካ ለምታስተናግደው የ2022 የዓለም ከ20 ዓመት በታች ዋንጫ ለማለፍ የአፍሪካ ሀገራት የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታዎችንን ሲከውኑ የሰነበቱ ሲሆን ወደ ሦስተኛው ዙር ያለፉ ሀገራትም በዚህኛው ሳምንት ወሳኝ መርሐ-ግብራቸውን ያደርጋሉ፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከነገ በስቲያ ቦትስዋናን ከሜዳዋ ውጪ የምትገጥም ሲሆን አራት ኢትዮጵያዊያን ሴት ኢንተርናሽናል ዳኞችም የፊታችን ዕረብ ምሽት 12፡00 ሰዓት ላይ ካምፓላ በሚገኘው ሴንት ሜሪ ስታዲየም ዩጋንዳ እና ደቡብ አፍሪካ የሚያደርጉት የማጣሪያ ጨዋታን በመሀል ዳኝነት የሚመሩ ይሆናል።
በዚህም ፀሀይነሽ አበበ የዚህ ዓመት ሁለተኛ ጨዋታዋን የምትመራ ሲሆን በተደጋጋሚ በማጣሪያ እና በሴካፋ ዋንጫ ሀገራችንን ወክለው ሲዳኙ የነበሩት ወይንሸት አበራ እና ይልፋሸዋ አየለ በረዳትነት መዳብ ወንድሙ በአራተኛ ዳኝነት ይህን ጨዋታ ለመምራት ዛሬ 6፡00 ሰዓት ላይ ወደ ስፍራው አምርተዋል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...