
በዓምላክ ተሰማ የኩዌት ሊግ ውድድሮችን ለመምራት ዛሬ ማታ ይጓዛል
ኢትዮጵያዊው ዓለምአቀፍ ዳኛ ባምላክ ተሰማ የኩዌት የሊግ ጨዋታዎች ለመምራት ወደ ስፍራው ያመራል።
በአህጉር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የተለያዩ ጨዋታዎችን የመራው ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ በዓምላክ ተሰማ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎችን እየመራ እንደነበር ይታወሳል። በአምስተኛ ሳምንት አዳማ ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ እንዲሁም ሲዳማ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረጉትን ጨዋታዎች የመራው አልቢትሩም የኩዌት እግርኳስ ማኅበር በፃፈው ደብዳቤ መሰረት የሀገሪቱን የውስጥ ውድድሮች ሊመራ መመረጡ ታውቋል።
በቀረበበት ክስ ከሰሞኑን የመነጋገሪያ ርዕስ የነበረው በዓምላክ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ታህሳስ 4 ድረስ የሚደረጉትን የኩዌት ኤስ ቲ ሲ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች በዳኝነት እና በቪ ኤ አራ ዳኝነት ለመምራት ዛሬ ማምሻውም ወደ ስፍራው እንደሚያቀና የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...
የአሠልጣኞች አስተያየት | ባህር ዳር ከተማ 1-0 ድሬዳዋ ከተማ
በወራጅ ቀጠናው ትልቅ ትርጉም ያለው ፍልሚያ በጣናው ሞገዶቹ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የአሸናፊ ቡድን አሠልጣኝ አስተያየት ሲሰጡ የተሸናፊው ግን ፍቃደኛ ሳይሆኑ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች
የሳምንቱን ፍልሚያዎች የሚያስጀምሩት የነገ ሁለት መርሐ-ግብሮች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ በ26ኛ ሳምንት በሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ...
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...