
በኢትዮጵያ ቡና እና ታፈሰ ሰለሞን ዙርያ አዲስ ነገር ተሰምቷል
ኢትዮጵያ ቡና የወራት ደሞዙ ላይ ቅጣት ቢያስተላልፍበትም ታቃውሞ ባሰማው ታፈሰ ሰለሞን ዙርያ ወቅታዊ መረጃ እናጋራችሁ።
ከቀናት በፊት ታፈሰ ሰለሞን ልምምድ ቦታ አለመገኘቱን ተከትሎ በቡድን መሪው አማካኝነት በቀረበው ሪፖርት መሠረት የወራት ደሞዙ እዳይከፈለው ውሳኔ መወሰኑ ይታወቃል። ይህን ውሳኔ ተቃውሞ ደብዳቤውን ያልተቀበለው ታፈሰ ሰለሞን በአንፃሩ የመልቀቂያ ደብዳቤ ለማስገባት ዝግጅት ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በነበረው ዘገባችን ገልፀን ነበር።
አሁን ባለው አዲስ መረጃ መሠረት የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ወልዴ እና ታፈሰ ሰለሞን ረፋድ ላይ ቢሮ ተገናኝተው የተነጋገሩ ሲሆን በዋናነት በተጫዋቹ እና በክለቡ መካከል መግባባት ላይ ተደርሶ ታፈሰ ሰለሞን ነገ ወደ ሀዋሳ በማቅናት ቡድኑን እንዲቀላቀል መስማማታቸው ታውቋል።
አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ታፈሰን አስመልክቶ “በቀጣይ የምናገኝበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል” በማለት ከጅማ አባ ጅፋር ጨዋታ መጠናቀቅ በኃላ መናገራቸው ይታወሳል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...