
ጅማ አባጅፋር የአሠልጣኝ ቡድን አባላቱ ላይ ደብዳቤ ፅፏል
በደረጃ ሰንጠረዡ ግርጌ ላይ የሚገኘው ጅማ አባጅፋር በወቅታዊ የክለቡ ውጤት ዙሪያ ለአሠልጣኝ ቡድን አባላቱ ደብዳቤ ፅፏል።
የ2010 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫ አሸናፊ ጅማ አባጅፋር የሊጉን ዋንጫ ከፍ ካደረገ በኋላ ወረድ ያሉ ውጤቶችን ከዓመት ዓመት እያስመዘገበ ይገኛል። በዘንድሮ የውድድር ዓመትም ስድስት ጨዋታዎችን አድርጎ አንዱንም ሳያሸንፍ በዘጠኝ የግብ ዕዳ 16ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በቅርቡ የሥራ-አስኪያጅ እና የቡድን መሪ ለውጥ ያደረገው ክለቡም ከትናንቱ የባህር ዳር ሽንፈት በኋላ ረዘም ያለ ስብሰባ ከተጫዋቾች እና ከአሠልጣኝ ቡድን አባላት ጋር ካደረገ በኋላ ከሰዓታት በፊት ለአሠልጣኝ ቡድን አባላቱ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መፃፉን ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች።
ለክለቡ ዋና አሠልጣኝ አሸናፊ በቀለ፣ ለምክትሎቹ ኢያሱ መርሐፅድቅ (ዶ/ር) እና የሱፍ ዓሊ፣ ለግብ ጠባቂዎች አሠልጣኝ መሐመድ ጀማል እንዲሁም ለክለቡ ወጌሻ ሰናይ ይልማ በተናጠል በተፃፈው ደብዳቤ ላይ ግለሰቦቹ በየድርሻቸው የተሰጣቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስቧል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...