
የዋልያዎቹ አሰልጣኞች ከፕሪምየር ሊግ አሰልጣኞች ጋር ይወያያሉ
የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና ረዳቶቻቸው ከፕሪምየር ሊግ አሰልጣኞች ጋር በነገው ዕለት በሀዋሳ ይወያያሉ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና ረዳቶቹ እየተመራ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ተሳትፏቸው ከምድባቸው ማለፍ ባይችሉም በጥር ወር በካሜሩን በሚዘጋጀው የአፍሪካ ዋንጫ የተሳትፎ ትኬቱን መቁረጡ ይታወሳል፡፡ ከሰሞኑ ሀዋሳ የሰነበቱት እና ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግን ሲከታተሉ የሰነበቱት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የአሰልጣኝ ቡድን አባላቱ በነገው ዕለት (ረቡዕ) አመሻሽ 11፡00 ላይ በሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ከአስራ ስድስቱ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች ዋና እና ረዳት አሰልጣኞች ጋር ለመወያየት ቀጠሮ መያዙን ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች፡፡
ውይይቱ ሊካሄድ የቻለበት ዋነኛ ምክንያት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ የምድብ የማጣሪያ ጨዋታዎች፣ በቀጣይ በጥር ወር ሀገራችን ተሳታፊ በምትሆንበት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ዝግጅት እንዲሁም የብሔራዊ ቡድኑ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ዙርያ ውይይት ለማድረግ እና ገንቢ ሀሳቦችን ለመሰብሰብ በማለም ይህ ፕሮግራም መዘጋጀቱን ድረ ገፃችን ተገንዝባለች፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...