
ሀዋሳ ከተማ የገንዘብ ቅጣት ተላለፈበት
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ በታዩ የዲሲፕሊን ጥሰቶች ላይ ውሳኔ ሲሰጥ ሀዋሳ ከተማ የገንዘብ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ተደርገው ከትናንት በስቲያ ዓርብ መጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ለካሜሩኑ የአፍሪካ ዋንጫ በሚል ለረጅም ጊዜ በእረፍት የሚዘልቀው ፕሪምየር ሊጉ በዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ በታዩ የዲሲፕሊን ጥሰቶች ላይ የሼር ካምፓኒው የውድድር እና ስነ ስርአት ኮሚቴ አሳልፏል፡፡ ሀዋሳ ከተማ በያዝነው ሳምንት የመጨረሻ የሳምንቱ መዝጊያ ጨዋታውን አድርጎ አርባምንጭ ከተማን 1ለ0 ከረታበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የክለቡ ደጋፊዎች እና የደጋፊ አስተባባሪዎች ከፖሊስ ጋር ግጭት ስለመፍጠራቸው እና ድንጋይ ስለመወርወራቸው እንዲሁም የተለያዩ የስታዲየሙ ንብረቶች ላይ ጉዳት ስለማድረሳቸው ሪፖርት በመቅረቡ ክለቡ የ75 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተላልፎበታል፡፡ ክለቡ በሚቀርብበት የዋጋ ተመን መነሻነት ንብረቱ ተሰልቶ ክፍያ እንዲፈፅምም በቅጣቱ ተካቷል፡፡
በተጫዋች ቅጣት ዜና ደግሞ ድሬዳዋ ከተማ ከ አዲስ አበባ ከተማ ሲጫወት በሁለት ቢጫ ከሜዳ የተወገደው አብዱለጢፍ መሀመድ እና በዚህው ጨዋታ ቀይ ካርድ ተመልክቶ የነበረው የአዲስ አበባ ከተማው ግብ ጠባቂ ዋኬኔ አዱኛ የአንድ ጨዋታ ቅጣት ሲጣልባቸው ዋኬኔ ተጨማሪ የ3 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ ሀዋሳ ከተማ አርባምንጭን 1ለ0 ሲያሸንፍ ግብ ካስቆጠረ በኋላ በውስጥ ልብሱ ሀይማኖታዊ ምስል አሳይቶ የነበረው ብሩክ በየነ የ3 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ሲተላለፍበት የባህርዳር ከተማው ግርማ ዲሳሳ ክለቡ በአዳማ በተረታበት ጨዋታ ቀይ በማየቱ የሦስት ጨዋታ የ3 ሺ ብር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ ሀዋሳ ከተማ እና ባህርዳር ከተማ ደግሞ እንደ ቡድን ባዩት የቢጫ ካርድ ብፋት የ5 ሺህ ብር ቅጣት ተላልፎባቸዋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...