
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ ነገ ስብስቡን ይቀላቀላል
ለካሜሩኑ የአፍሪካ ዋንጫ ዝግጅቱን በስፍራው እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግዙፉን አጥቂ ነገ ያገኛል።
በ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ ጥሪ ካቀረበላቸው 28 ተጫዋቾች መካከል 25ቱን በመያዝ ያሳለፍነው እሁድ ለዝግጅት ወደ ስፍራው ማቅናቱ ይታወቃል። ያውንዴ በሚገኘው ዴ ዱፒዮቴ ሆቴል ማረፊያውን በማድረግ ልምምዱን ሲሰራ የነበረው ቡድኑም በህመም ምክንያት ይዞት ወደ ስፍራው ያላቀናውን መናፍ ዐወል በመተው ለአህመድ ረሺድ ጥሪ ያቀረበ መሆኑን ቀድመን የዘገብን ሲሆን ተጫዋቹም በነገው ዕለት ወደ ስፍራው የሚያቀና ይሆናል። ከሰዓታት በፊት ደግሞ በግብፁ አል ጉውና የሚጫወተው ሽመልስ በቀለ ስብስቡን እንደተቀላቀለ የገለፅን ሲሆን የቀረው ብቸኛው ተጫዋች ሙጂብ ቃሲም ደግሞ ነገ ወደ ካሜሩን እንደሚጓዝ ድረ-ገፃችን አውቃለች።
በአልጄሪያው ጄኤስ ካቢሌ የሚጫወተው ሙጂብ እንደ ሽመልስ አዲስ አበባ መምጣት ሳይጠበቅበት በቱርክ ኢስታምቡል አድርጎ ወደ ካሜሩን እንደሚያቀናም ለማወቅ ችለናል። ተጫዋቹ ዘግይቶ ስብስቡን በመቀላቀሉም ከነገው የሱዳን የአቋም መለኪያ ጨዋታ ውጪ እንደሆነ ተነግሯል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...