
ዋልያው አምስት ተጫዋቾችን እና ሦስት የአሠልጣኝ ቡድን አባላቱን ዛሬ አያገኝም
ምሽት 12:30 ከሱዳን አቻው ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ የሚያደርገው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምስት ተጫዋቾችን እና ሦስት የአሠልጣኝ ቡድን አባላቱን በጨዋታው እንደማያገኝ ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
በካሜሩኑ አስተናጋጅነት በሚከናወነው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከቀናት በፊት ወደ ስፍራው በማቅናት ልምምዱን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። ብሔራዊ ቡድኑም በዛሬው ዕለት የመጀመሪያ የአቋም መፈተሻ ጨዋታውን ከሱዳን አቻው ጋር ከደቂቃዎች በፊት የሚያከናውን ይሆናል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ብሔራዊ ቡድኑ በኮቪድ-19 ምክንያት አምስት ተጫዋቾችን እና ሦስት የአሠልጣኝ ቡድን አባላቱን በጨዋታው እንደማያገኝ ሶከር ኢትዮጵያ ከምንጮቿ አረጋግጣለች። ለተጫዋቾቹ እና አሠልጣኞቹ የግል መብት ስንል ስማቸውን ከመጥቀስ ብንቆጠብም ግለሰቦቹ በአሁኑ ሰዓት ራሳቸውን አግለው እንደሚገኙም ለማወቅ ችላናል።
በጉዳዩ ላይ የሚኖሩ አዳዲስ ነገሮችን እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...