
ድሬደዋ ዋና አሠልጣኙን ገምግሞ ውሳኔ አሳልፏል
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወጥ አቋም ማሳየት ያልቻለው ድሬደዋ ከተማ በዛሬው ዕለት አሰልጣኙን በመገምገም የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
የድሬዳዋ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የቡድኑ የአሰልጣኝ አባላት በተገኙበት ዛሬ ረጅም ሰዓት የፈጀ እና በዘጠኝ ሳምንታት ውስጥ የቡድኑ ጠንካራ እንዲሁም ደካማ ጎን ምን ይመስል እንደነበረ ጥልቅ ግምገማ ተደርጓል። በግምገማው በርከት ያሉ አስገራሚ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን በዋናነት ደግሞ በዋና አሠልጣኙ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ ላይ የአሠልጣኝነት ብቃት ላይ ጥያቄዎች ተነስተው ቦርዱ ውሳኔ ማሳለፉን ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
በዚህም መሠረት ከዚህ በኋላ በሚኖሩ ቀሪ ጨዋታዎች የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ የክለቡን የውጤት ችግር ይቀረፋል ብሎ ቦርዱ የማያምን መሆኑን በመግለፅ አሰልጣኝ ዘማርያም ታግደው እንዲቆዩ ከውሳኔ ላይ ተደርሷል።
ሶከር ኢትዮጵያ በክለቡ እና በአሰልጣኝ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ ዙርያ የሚኖሩ አዳዲስ ነገሮችን ተከታትለን እናቀርባለን።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...