
ሀዲያ ሆሳዕና በአንድ ተጫዋች ጉዳይ የፍርድ ቤት ውሳኔ ተላለፈበት
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከተጫዋቾች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ክሶች ሲሰሙበት የቆየው ሀዲያ ሆሳዕና የፍርድ ቤት ውሳኔ ተወስኖበታል።
የቀድሞ ተጫዋቹ አብዱልሰመድ ዓሊ ”የማትጊያ አምስት መቶ ሰማንያ ሺህ ብር በቼክ ቢሰጠኝም የሀዲያ ሆሳዕና እግርኳስ ክለብ ሊከፍለኝ አልቻለም።” በማለት በ2013 መጋቢት ወር ላይ በአቶ ብርሐኑ በጋሻው የሕግ አማካሪ ጠበቃ እና የአግር ኳስ ስፖርትኞች ሕጋዊ ወኪል አማካኝነት በመደበኛ ፍርድ ቤት ክስ ተመስርቷል።
ተከሳሽ ሀዲያ ሆሳዕና እግርኳስ ክለብ ምላሽ እንዲሰጥ በፍርድ ቤት በኩል በተለያዩ መንገዶች የቀጠሮ ቀን ጥሪ ቢደረግላቸውም መገኘት ባለመቻላቸው ሐምሌ ወር 2013 በዋላው ችሎት ውሳኔ ክለቡ ለተጫዋቹ ከላይ የተጠቀሰውን የገንዘብ መጠን እንዲከፍል ውሳኔ አሳልፎበታል።
ሆኖም ክለቡ የተወሰነውን ውሳኔ ተግባራዊ አለማድረጉን ተከትሎ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ካምፓኒ ሀዲያ ሆሳዕና ከሚያገኘው ገቢ በመቁረጥ በአምስት ቀናት ውስጥ ተፈፃሚ እንዲያደርግ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...