
ዋልያው ተጨማሪ አንድ ተጫዋች በነገው ጨዋታ ላያገኝ ይችላል
ከሰዓታት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሽመልስ በቀለን በነገው ጨዋታ እንደማያገኝ ያስነበብን ሲሆን ተጨማሪ አንድ ተጫዋችም በጉዳት የመሰለፉ ነገር አጠራጣሪ ሆኗል።
በጉጉት የሚጠበቀው 33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር በነገው ዕለት በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ካሜሩን ሲጀመር በምድብ አንድ ከአዘጋጇ ካሜሩን፣ ኬፕ ቨርድ እና ቡርኪና ፋሶ ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም በመክፈቻው ቀን ሁለተኛ ጨዋታ የኬፕ ቨርድ አቻውን ይገጥማል። በስብስቡ ውስጥ ከኮቪድ ጋር ተያይዞ ምንም አሉታዊ ዜና ባይሰማም መጠነኛ የጉዳት ጉዳዮች እየተነሱ ይገኛሉ።
በግብፁ ክለብ አል ጎውና የሚጫወተው ሽመልስ ከጡንቻ ጋር ተያይዞ ጉዳት ማስተናገዱን እና ለነገው ጨዋታ መድረሱ አጠራጣሪ መሆኑን ቀድመን ያስነበብን ሲሆን አሁን በደረሰን መረጃ ደግሞ የአዳማ ከተማው አጥቂ ዳዋ ሁቴሳም መጠነኛ የቁርጭምጭሚት ጉዳት አስተናግዷል። የዳዋ ጉዳት ያን ያህል ለክፉ የሚሰጥ ባይሆንም እንደ ሽመልስ የእርሱም መሰለፍ አጠራጣሪ መሆኑ ተመላክቷል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ዋልያዎቹ ፈርዖኖቹን አንበርክከዋል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታው ማላዊ ላይ ግብፅን ገጥሞ ከሙሉ የጨዋታ ብልጫ ጋር 2-0 መርታት ችሏል።...
የዋልያዎቹ እና ፈረኦኖቹን ጨዋታ የሚመሩ ዳኞች ታውቀዋል
ነገ ምሽት በኢትዮጵያ እና ግብፅ መካከል የሚደረገውን ተጠባቂ ጨዋታ የሚመሩ አልቢትሮች ታውቀዋል። የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ነገም ሲቀጥሉ በምድብ...
የዋልያዎቹ አሠልጣኝ እና አምበል ከወሳኙ ጨዋታ በፊት ሀሳብ ሰጥተዋል
👉"የሳላ መኖር እና አለመኖር የእኛ እቅድ ላይ ምንም ተፅዕኖ አያደርግም" ውበቱ አባተ 👉"ከምድባችን ለማለፍ በምናደርገው ጉዞ የነገው ጨዋታ ወሳኝ ነው"...
ሱራፌል ዳኛቸው ለነገው ጨዋታ ይደርስ ይሆን ?
ነገ ምሽት የግብፅ ብሔራዊ ቡድንን የሚገጥመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አማካዩን ሊያጣ ይችላል። የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዎች በአህጉራችን የተለያዩ...
“ዓላማችን ቀጣዩ የአፍሪካ ዋንጫ ላይ መሳተፍ ነው” አቡበከር ናስር
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወሳኝ አጥቂ የሆነው አቡበከር ናስር ከነገው ጨዋታ በፊት ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር አጠር ያለ ቆይታ አድርጓል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
የዋልያዎቹ አሰልጣኝ እና አምበል ከነገው ጨዋታ በፊት አስተያየት ሰጥተዋል
ዋልያዎቹ ነገ ከማላዊ ጋር የመጀመሪያ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ ሲጠበቅ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና አምበሉ ሽመልስ በቀለ ከመገናኛ ብዙሀን...