
ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊው ዋልያውን አበረታተዋል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከማድረጉ በፊት የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ ቡድኑን አነቃቅተዋል።
33ኛው የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ ውድድር በ24 ተሳታፊዎች መካከል ሊደረግ የሰዓታት እድሜ ብቻ ቀርቶታል። ብሔራዊ ቡድናችንም የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታውን ከኬፕ ቨርድ አቻው ጋር ምሽት አራት ሰዓት ላይ በኦልምቤ ስታዲየም ያከናውናል። በጁዩጋ ፓላስ ሆቴል ማረፊያቸውን አድርገው የጨዋታውን መጀመር እየተጠባበቁ የሚገኙት የቡድኑ ተጫዋቾች እና የአሠልጣኝ ቡድን አባላትም በኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጀላ መርዳሳ የማበረታቻ ንግግር እንደተደረገላቸው አውቀናል።
ክቡር ሚኒስትሩ በበይነመረብ አማካኝነት በዙም ከቡድኑ ጋር ቆይታ ሲያደርጉም መልካም ዕድል እንዲገጥማቸው ተመኝተው ተጫዋቾች እና አሠልጣኞች ሀገራቸውን እንዲያስጠሩ አደራ ብለዋል። በአሁኑ ሰዓትም የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳይያያይ ጂራ በተጨማሪነት ቡድኑን ለማበረታታት ስብስቡ ያረፈበት ሆቴል እንደደረሱ አውቀናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...