
የአፍሪካ ዋንጫ ልዩ ዘገባ ከካሜሩን | ሽመልስ በቀለ ለሐሙሱ ጨዋታ ይደርስ ይሆን ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለሐሙሱ ጨዋታ ልምምዱን የቀጠለ ሲሆን ሽመልስ በቀለ የዛሬውን ልምምድ አቋርጦ ሲወጣ ተመልክተናል።
በሽመልስ በቀለ የጉዳት ሁኔታን አስመልክቶ በትናንትናው ዘገባችን በሦስት ምዕራፍ የተከፈሉ ልምምዶችን በተሳካ ሁኔታ እንዳጠናቀቀ እና የተለየ ነገር ካልተፈጠረ በቀር ለካሜሩን ጨዋታ እንዲደርስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀን ነበር። በዛሬው የልምምድ መርሐግብሩን በጥሩ ሁኔታ እያከናወነ ይገኝ የነበረው ሽመልስ ለሁለት ተክፍሎ በተደረገው ጨዋታ ላይ የጡንቻ መሳሳብ ጉዳቱ አገርሽቶበት በሀዘን ስሜት ልምምዱን አቋርጦ ወጥቷል።
ከክስተቱ በኋላ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ኢሳይያስ ጂራ ሲያፅናኑት የታዩ ሲሆን የቡድን አጋሮቹ ጀማል ጣሰው እና ጌታነህ ከበደም ሲያረጋጉት ተመልክተናል። ከከልምምዱ መጠናቀቅ በኋላ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከአሰልጣኝ አባላቶቻቸው ጋር በመሆን የህክምና ቡድኑን በመጥራት ሽመልስ በተገኘበት በጉዳቱ ዙርያ ውይይት አድርገዋል። የውይይቱ መጨረሻ ምን አንደሆነ ለጊዜው መረጃ ባናገኝም ለቀጣይ ጨዋታ ሽመልስ የመድረሱ ነገር አጠራጣሪ አድርጎታል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሀዲያ ሆሳዕና የዕግድ ውሳኔ ተላለፈበት
ሀዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም በይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተሰጠበትን ውሳኔ ተግባራዊ አላደረገም በሚል የዕግድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ለ15 ተጫዋቾች...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...