
ከፍተኛ ሊግ | ሀላባ ከተማ አዲስ አሠልጣኝ ቀጥሯል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ስር የሚገኘው ሀላባ ከተማ አሰልጣኝ አላምረው መስቀሌን በማሰናበት አዲስ አሠልጣኝ በቦታው ተክቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የ2014 የውድድር አመትን በአሰልጣኝ አላምረው መስቀሌ እየተመራ በምድብ ሀ በሆሳዕና ከተማ በነበረው የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች ላይ ተካፋይ የነበረው ሀላባ ከተማ ከዘጠኝ የዙሩ ጨዋታዎች በስምንት ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ በመቀመጡ የክለቡ የበላይ አካላት ባደረጉት ውይይት አሰልጣኙን ከቦታው በማንሳት በምትኩ አዲስ አሰልጣኝ መርጧል፡፡ ቾንቤ ገብረህይወትም አዲሱ የክለቡ አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል፡፡
ከሀዋሳ ከተማ የታዳጊ ቡድን የጀመረው የአሰልጣኝነት ዘመኑ በመቀጠል በሲዳማ ቡና ረዳት እና ጊዜያዊ አሰልጣኝ እንዲሁም ደግሞ ደቡብ ፖሊስን በዋና አሰልጣኝነት አሰልጥኖ አልፏል፡፡ እስከ አምናው የውድድር ዓመት ድረስ ነቀምቴ ከተማን ለአራት ዓመታት በማሰልጠን ቆይታ የነበረው አሰልጣኙ ሀላባ ከተማን በሁለተኛው ዙር የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎች በዋና አሰልጣኝነት ለመምራት መሾሙን ክለቡ ለሶከር ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...
የአሠልጣኞች አስተያየት | ባህር ዳር ከተማ 1-0 ድሬዳዋ ከተማ
በወራጅ ቀጠናው ትልቅ ትርጉም ያለው ፍልሚያ በጣናው ሞገዶቹ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ በኋላ የአሸናፊ ቡድን አሠልጣኝ አስተያየት ሲሰጡ የተሸናፊው ግን ፍቃደኛ ሳይሆኑ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች
የሳምንቱን ፍልሚያዎች የሚያስጀምሩት የነገ ሁለት መርሐ-ግብሮች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ በ26ኛ ሳምንት በሀዋሳ ከተማ እና አርባምንጭ...
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...