
ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ ቡድናቸውን ይመራሉ
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
በአፍሪካ ዋንጫው በካፍ የቴክኒካል ቡድን አባል በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።
በካሜሩኑ የ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ላይ ካፍ አሉኝ ከሚላቸው 24 ኤሊት ኢንስትራክተሮች መካከል አንዱ የነበሩት አብርሀም መብራቱ ከግብፁ የአፍሪካ ዋንጫ በመቀጠል ለሁለተኛ ጊዜ በካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የካፍ የቴክኒካል አባላት በመሆን እስከ አፍሪካ ዋንጫው ፍፃሜ ድረስ አገልግለዋል።
በአፍሪካ ዋንጫውን የቴክኒክ ሂደት ከአጋሮቻቸው ጋር ከገመገሙ በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫን በመጨረሻው የፍፃሜ ጨዋታ ማግስት ሰጥተው የነበሩት ኢንስትራክተሩ በትላንትናው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። በመቀጠል በቀጥታ ወደ ድሬዳዋ አምርተው በዛሬው ዕለት ክለባቸውን የመጀመሪያ ልምምድን አሰርተዋል፡፡
ያለፉትን ሁለት ጨዋታዎች (ከሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ) በረዳት አሰልጣኙ አብረሀም መላኩ መሪነት የተጫወተው ባህርዳር ከተማ በ14 ነጥቦች 9ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን ነገ ሐሙስ ምሽት 01፡00 ላይ በዋና አሰልጣኙ እየተመራ ሀዋሳ ከተማ ይገጥማል ፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ሪፖርት | የወራጅ ቀጠናው ተጠባቂ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ለዓይን ሳቢ የነበረው የአዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ 1-1 መጠናቀቁን ተከትሎ ባህር ዳር ከተማ እና መከላከያ በሊጉ መቆየታቸውን ሲያረጋግጡ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | መከላከያ 1-2 ሀዋሳ ከተማ
ሀዋሳ ከተማ ከመመራት ተነስቶ በማሸነፍ በሦስተኛነት ፉክክሩ ከቀጠለበት ጨዋታ በኋላ ተጋጣሚ አሰልጣኞች ይህንን ብለዋል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ - መከላከያ ስለሁለቱ...
ሪፖርት | ሀዋሳ ከተማ መከላከያን አሸንፏል
ሀዋሳ ከተማዎች ደካማ በነበሩበት ጨዋታ አስፈላጊውን ሦስት ነጥብ ከመከላከያ መንጠቅ ችለዋል። መከላከያዎች በመጨረሻው የጨዋታ ሳምንት ከአዳማ ጋር ያለግብ አቻ ከተለያየው...