
የ20 ዓመት በታች ውድድሩ ተራዝሟል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
ባሳለፍነው ሳምንት የዕጣ ማውጣት ሥነስርዓት የተከናወነለት ውድድር መጀመሪያ ላይ ለውጥ ተደርጓል።
የ2014 የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ታዳጊ ወጣቶች ፕሪምየር ሊግ በ19 ክለቦች መካከል እንደሚካሄድ ይጠበቃል። ውድድሩ በሁለት ምድብ ተከፍሎ ምድብ ሀ በጎንደር ምድብ ለ ደግሞ በአሰላ እንደሚደረግ ባሳለፍነው ሳምንት በጁፒተር ሆቴል በተከናወነው የዕጣ ማውጣት ሥነስርዓት ላይ መወሰኑም አይዘነጋም።
በመጀመሪያ እንደነበረው ውጥን ይህ ውድድር ከየካቲት 12 ጀምሮ በሁለቱ ከተሞች እንደሚካሄድ እየተጠበቀ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ፌዴሬሽኑ ባሳወቀው መሰረት ግን ቀኑ ለውጥ ተደርጎበታል። በዚህም መሰረት የተወሰኑ ክለቦች MRI ምርመራ በመጨረስ ውል ያላጠናቀቁ በመሆናቸው ሳቢያ የውድድሩ የመጀመሪያ ቀን ወደ የካቲት 19 ተገፍቷል። ለውድድሩ መራዘም ምክንያት ከሆነው ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘም ፌዴሬሽኑ ክለቦች እስከ የካቲት 15 ድረስ ውላቸውን እንዲያጠናቅቁ አሳስቧል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ፌዴሬሽኑ የሻረውን ኃላፊነት ለሊግ ካምፓኒው መልሶ ሰጥቷል
ከሰሞኑ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የነበሩት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር ወደ ስምምነት መጥተዋል። የወልቂጤ ከተማው አምበል ጌታነህ...
ፌዴሬሽኑ ለፕሪሚየር ሊጉ አክስዮን ማህበር የሰጠውን ኃላፊነት ሽሯል
ወቅታዊ የእግርኳሱ ርዕስ በሆነው የጌታነህ ከበደ ጉዳይ መነሻነት የእግርኳሱ የበላይ አካል የሆነው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለፕሪሚየር ሊጉ አክስዮን ማህበር የሰጠውን...
ጌታነህ ከበደ ቅጣቱ ተሽሮለታል
በ25ኛው ሳምንት ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በተደረገ ጨዋታ ቅጣት ተላልፎበት የነበረው የወልቂጤ ከተማው አምበል ወደ ሜዳ ይመለሳል። ወልቂጤ ከተማ ሀዲያ...
የፌዴሬሽኑ ምርጫ የሚደርግበት ወቅት ታውቋል
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት የሚመራውን ፕሬዝዳንት እና የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ምርጫ ለማከናወን የሚደረግበት ወቅት ይፋ ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ...
“የግብፅ እግርኳስ ፌዴሬሽን ‘ሙሉ ወጪያችሁን ችዬ ካይሮ ላይ ተጫወቱ’ ብሎን ነበር” ባህሩ ጥላሁን
👉 "የግብፅ ጨዋታ የአባይ መነሻ በሆነው ቦታ ላይ ቢደረግ ያለው ትርጉም ግልፅ ነው" 👉"ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ባለመኖሩ ዋጋ እየከፈለ የሚገኘው...
ወላይታ ድቻ የ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ቻምፒዮን ሆኗል
ዛሬ አዳማ ላይ በተደረጉ የ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ ማጠቃለያ ጨዋታዎች አርባምንጭ ከተማ የደረጃ ወላይታ ድቻ ደግሞ የፍፄሜ ጨዋታዎችን አሸንፈዋል።...