
የወልቂጤ ከተማ እና የሲዳማ ቡናን ጨዋታ የመሩት ረዳት ዳኛ ከውድድሩ ተሰናብተዋል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
ባሳለፍነው ሳምንት የተደረገውን የወልቂጤ ከተማ እና የሲዳማ ቡናን ጨዋታ ከመሩት ዳኞች መሐል አንዱ የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
በዘንድሮ የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ውድድር ላይ እየታዩ ካሉ ክፍተቶች መካከል በተለየ መልኩ ረዳት ዳኞች የሚፈፅሙት ተደጋጋሚ የውሳኔ አሰጣጥ ክፍተት በጉልህ ይነሳል፡፡ በተጠናቀቀው የ13ኛ ሳምንት የፕሪምየር ሊጉ መርሐ-ግብር ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ተገናኝተው ያለ ጎል አቻ መለያየታቸው ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ በዕለቱ ወልቂጤ ከተማ በመጀመሪያ አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአማካዩ በሀይሉ ተሻገር አማካኝነት ግብ አስቆጥሮ የነበረ ቢሆንም በጨዋታው በክቡር ትሪቡን በኩል በረዳት ዳኝነት ተሰይመው ጨዋታውን የመሩት እና ረጅም ዓመታትን በፌዴራል ረዳት ዳኝነት ያገለገሉት ዳንኤል ጥበቡ ግቧ ከጨዋታ ውጪ ነች በማለት ሽረው ነበር። ረዳት ዳኛው ግቧን በመሻራቸው የዳኞች ኮሚቴ ጉዳዩን ከገመገመ በኋላ ዳኛውን ከውድድሩ በማገድ ከድሬዳዋ አሰናብቷቸዋል፡፡
በቀሩት የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ላይ ጥፋት የሚፈፅሙ ዳኞች ተመሳሳይ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ይጠበቃል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የአሰልጣኞች አስተያየት | መከላከያ 0-0 አዳማ ከተማ
የሳምንቱ ማሳረጊያ ጨዋታ ያለ ጎል ከተጠናቀቀ በኋላ አሰልጣኞች ድህረ ጨዋታ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ - መከላከያ ስለ ጨዋታው...? "በመጀመሪያው...
ሪፖርት | መከላከያ እና አዳማ ያለግብ ተለያይተዋል
28ኛው ሳምንት ደካማ ፉክክር በታየበት እና 0-0 በተጠናቀቀው የመከላከያ እና አዳማ ከተማ ጨዋታ ተቃጭቷል። መከላከያ ከወላይታ ድቻ ያለግብ ከጨረሰበት ጨዋታ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ፋሲል ከነማ 1-0 ሀዋሳ ከተማ
ፋሲል ከነማዎች ወሳኝ ድል ካስመዘገቡበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ - ፋሲል ከነማ...
ሪፖርት | ዐፄዎቹ ከመሪው ያላቸው የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ቀንሰዋል
እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የፋሲል ከነማ እና የሀዋሳ ከተማ ጨዋታ ፋሲሎች በመጂብ ቃሲም ብቸኛ ግብ በድል መወጣታቸውን ተከትሎ ከቅዱስ ጊዮርጊስ...
የአሠልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 1-0 ኢትዮጵያ ቡና
በአህመድ ሁሴን ብቸኛ ግብ አርባምንጭ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን ከረታበት ጨዋታ በኋላ አሠልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል። መሳይ ተፈሪ - አርባምንጭ ከተማ ስለተከታታይ...