
የምንተስኖት አዳነ እና የአዳማ ከተማ ጉዳይ ዕልባት አግኝቷል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
ያለፉትን ወራት ከክፍያ ጋር በተገናኘ ውዝግብ ውስጥ ገብተው የሰነበቱት አዳማ ከተማ እና ምንተስኖት አዳነ ጉዳያቸው መቋጫ አግኝቷል።
የአማካይ መስመር ተጫዋቹ ምንተስኖት አዳነ በያዝነው ዓመት መስከረም ወር ላይ አዳማ ከተማን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከተቀላቀለ በኋላ ከቅድመ ክፍያ እና ከደመወዝ ጋር በተገናኘ ውዝግብ ውስጥ በመግባት ሲካሰስ መሰንበቱ ይታወቃል። አሁን ባገኘነው መረጃ ምንተስኖት አዳነ እና ክለቡ በፌዴሬሽኑ አሸማጋይነት በዛሬው ዕለት በስምምነት መለያየታቸውን ይጠቁማል።
ከአዳማ ከተማ ጋር እምብዛም ጨዋታዎች ሳያደርግ ያሳለፈው አማካዩ ከሰሞኑ ወደ አንድ የፕሪምየር ሊጉ ክለቡ ለማምራት በሂደት ላይ መሆኑንም ጭምር ሰምተናል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሪፖርት | ሙጂብ እና ሱራፌል ከ20 ሳምንታት በኋላ ዐፄዎቹ የሊጉን መሪነት እንዲረከቡ አድርገዋል
ፋሲል ከነማ በሙጂብ ቃሲም እና ሱራፌል ዳኛቸው ጎሎች ታግዞ ቅዱስ ጊዮርጊስ እስኪጫወት ድረስ የሊጉ መሪ ሆኗል። ባሳለፍነው ሳምንት ሀዋሳ ከተማን...
ቅድመ ዳሰሳ | የ29ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች
የነገውን ተጠባቂ የጨዋታ ቀን የተመለከተው ዳሰሳችን እንዲህ ይነበባል። ወደ ፍፃሜው እየቀረበ በሚገኘው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ነገ እጅግ አጓጊ የሆነ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ባህርዳር ከተማ 1-1 ሰበታ ከተማ
የዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ክለብ አሰልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ - ባህርዳር ከተማ ስለ ሁለቱ...
ሪፖርት | በሁለቱ አጋማሾች የተቆጠሩት ድንቅ ጎሎች ባህር ዳር እና ሰበታን ነጥብ አጋርተዋል
በዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ እና ሰበታ ከተማ በውብ ግቦቻቸው አንድ እኩል ወጥተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ድሬዳዋ ከተማን አንድ ለምንም...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ሀዲያ ሆሳዕና 2-2 ወላይታ ድቻ
ከጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር በኋላ ሁለት አቻ ከተጠናቀቀው ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት...
ሪፖርት | ወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ነጥብ ተጋርተዋል
ጥሩ ፉክክር ያስተናገደው የምሳ ሰዓቱ የወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ 2-2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከቅዱስ ጊዮርጊሱ ጨዋታ...