
በዓምላክ ተሰማ ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ሁለት ጨዋታዎችን ይመራል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች በርካታ ጨዋታዎችን የመራው ኢትዮጵያዊው አርቢትር ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎችን እንዲመራ ተመድቧል።
በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ የመሐል ዳኞች መካከል አንዱ የሆነው በዓምላክ ተሰማ በካሜሩን አስተናጋጅነት በተከናወነው 33ኛው የአህጉሪቱ ውድድር አስደናቂ ብቃት በማሳየት ከብዙዎች አድናቆት ሲቸረው እንደነበር አይዘነጋም። የ41 ዓመቱ አርቢትር አሁንም ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ጨዋታዎችን መምራት ቀጥሎ የፊታችን ቅዳሜ እና መጋቢት 16 የሚደረጉትን ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎችን በመሐል አልቢትርነት እንዲከውን መመደቡን ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
ቅዳሜ የሚደረገው ጨዋታ የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ውድድር ሲሆን ተፋላሚዎቹም ማሜሎዲ ሰንዳውንስ እና አል አህሊ ናቸው። ደቡብ አፍሪካ ላይ የሚደረገውን ይህንን ጨዋታ ለመምራት አልቢትሩ ነገ ወደ ስፍራው እንደሚያመራም ሰምተናል።
መጋቢት 16 የሚደረገው ሁለተኛ ጨዋታ ደግሞ በኳታሩ ዓለም ዋንጫ አፍሪካን የሚወክሉ አምስት ቡድኖችን ከሚለዩ መርሐ-ግብሮች መካከል አንዱ ነው። እሱም ባማኮ ላይ ማሊ እና ቱኒዚያ የሚያደርጉት የመጨረሻ ዙር የመጀመሪያ መርሐ-ግብር ነው።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...