
አዲስ አበባ ከተማ አጥቂ ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
ከሰሞኑን ከሁለት ተጫዋቾች ጋር በስምምነት የተለያየው አዲስ አበባ ከተማ በዝውውር መስኮቱ የመጀመሪያ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል።
በአሠልጣኝ ደምሰው ፍቃዱ የሚመራው አዲስ አበባ ከተማ ሊጉ በቀጣይ የሚደረግበት አዳማ ከተማ ቀድሞ በመግባት ዝግጅቱን እያከናወነ ሲገኘ ከአማካዩ ጋብሬል አህመድ እና የመስመር ተጫዋቹ ያሬድ ሀሰን ጋር በስምምነት እንደተለያየ መዘገባችን ይታወሳል። በክፍት ቦታዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ሲጥር የነበረው ክለቡም ከሰበታ ከተማ ጋር የተለያየውን ተስፋ የተጣለበት አጥቂ መሐመድ አበራን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል።
መሐመድ ከመከላከያ ተስፋ ቡድን 2012 ላይ ካደገ በኋላ ጥሩ እንቅስቃሴ በማድረግ የዘንድሮ የውድድር ዓመት ከመጀመሩ በፊት ወደ ሰበታ ከተማ ዝውውር ፈፅሞ ነበር። ተጫዋቹ ከረጅም ጉዳት በኋላ ወደ ሜዳ ቢመለስም በ15 ሳምንታት የሊጉ ጉዞ ከ99 ደቂቃዎች በላይ ክለቡን ማገልገል ሳይችል ከቀናት በፊት በስምምነት ተለያይቶ ነበር። የወረቀት ስራዎች ባይጠናቀቁም ተጫዋቹ በአሁኑ ሰዓት ስብስቡን በመቀላቀል አዳማ ላይ ልምምዱን እየሰራ እንደሚገኝ አውቀናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ሪፖርት | መከላከያ እና አዳማ ያለግብ ተለያይተዋል
28ኛው ሳምንት ደካማ ፉክክር በታየበት እና 0-0 በተጠናቀቀው የመከላከያ እና አዳማ ከተማ ጨዋታ ተቃጭቷል። መከላከያ ከወላይታ ድቻ ያለግብ ከጨረሰበት ጨዋታ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዲስ አበባ ከተማ 4-3 ሰበታ ከተማ
አዲስ አበባን ባለ ድል ካደረገው እና ሰበታ ከተማ ከጅማ አባ ጅፋር ጋር ተያይዞ መውረዱን ካረጋገጠበት ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች አስተያየት...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች
ነገ ቀጥለው በሚደረጉት የሊጉ ሦስት ጨዋታዎች ዙሪያ ተከታዮቹን ነጥቦች አንስተናል። ጅማ አባ ጅፋር ከ ወላይታ ድቻ የጨዋታ ቀኑ ረፋድ ላይ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...