
ሁለገቡ ተጫዋች ባህርዳር ከተማን ለመቀላቀል ተስማማ
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
የጣና ሞገዶቹ በዝውውሩ የመጀመሪያ ተጫዋች የግላቸው ለማድረግ ተስማምተዋል፡፡
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 የውድድር ዘመን በአሰልጣኝ አብርሀም መብራቱ እየተመራ የሚገኘው ባህርዳር ከተማ በሁለተኛው ዙር የሊጉ ውድድር በመጀመሪያው ዙር ላይ የገጠመውን ጉድለት ለመድፈን እና ተጠናክሮ ለመቅረብ ይረዳው ዘንድ ሁለገቡን ተጫዋች ሄኖክ ኢሳይያስን ወደ ስብስቡ ለመቀላቀል ስምምነት ላይ ደርሷል።
የቀድሞው የደደቢት፣ ጅማ አባ ጅፋር፣ ወላይታ ድቻ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ከ2012 አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ ለድሬዳዋ ከተማ በአማካይ ተከላካይ እና በመስመር ተከላካይነት እየተጫወተ የነበረው ሄኖክ ከምስራቁ ክለቡ ጋር ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ባህርዳር ከተማን ምርጫው አድርጓል፡፡ ተጫዋቹ በአሁኑ ሰአት ከክለቡ ጋር የሚገኝ ሲሆን አመሻሹን የጣና ሞገደኞቹን በይፋ የሚቀላቀልም ይሆናል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአሰልጣኞች አስተያየት | መከላከያ 0-0 አዳማ ከተማ
የሳምንቱ ማሳረጊያ ጨዋታ ያለ ጎል ከተጠናቀቀ በኋላ አሰልጣኞች ድህረ ጨዋታ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ - መከላከያ ስለ ጨዋታው...? "በመጀመሪያው...
ሪፖርት | መከላከያ እና አዳማ ያለግብ ተለያይተዋል
28ኛው ሳምንት ደካማ ፉክክር በታየበት እና 0-0 በተጠናቀቀው የመከላከያ እና አዳማ ከተማ ጨዋታ ተቃጭቷል። መከላከያ ከወላይታ ድቻ ያለግብ ከጨረሰበት ጨዋታ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ፋሲል ከነማ 1-0 ሀዋሳ ከተማ
ፋሲል ከነማዎች ወሳኝ ድል ካስመዘገቡበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ - ፋሲል ከነማ...
ሪፖርት | ዐፄዎቹ ከመሪው ያላቸው የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ቀንሰዋል
እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የፋሲል ከነማ እና የሀዋሳ ከተማ ጨዋታ ፋሲሎች በመጂብ ቃሲም ብቸኛ ግብ በድል መወጣታቸውን ተከትሎ ከቅዱስ ጊዮርጊስ...
የአሠልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 1-0 ኢትዮጵያ ቡና
በአህመድ ሁሴን ብቸኛ ግብ አርባምንጭ ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን ከረታበት ጨዋታ በኋላ አሠልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል። መሳይ ተፈሪ - አርባምንጭ ከተማ ስለተከታታይ...
ሪፖርት | በአቡበከር የመጨረሻ ጨዋታ አዞዎቹ ቡናማዎቹን ረተዋል
አርባምንጭ ከተማዎች በውድድር ዓመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ያሸነፉበትን ውጤት ኢትዮጵያ ቡና ላይ አስመዝግበዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ከድሬዳዋ ከተማ ሦስት...