​ባህር ዳር ከተማ በይፋ ሄኖክ ኢሳይያስን አስፈረመ

[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]

ከሰዓታት በፊት በሰራነው ዘገባ ሔኖክ እና ባህር ዳር ስምምነት መፈፀማቸውን አመላክተን የነበረ ሲሆን አሁን ሁለቱ አካላት ስምምነታቸው ይፋ አድርገዋል።

በአሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ የሚመራው ባህርዳር ከተማ በሁለተኛው ዙር ውድድር ተጠናክሮ ለመቅረብ በዝውውር መስኮቱ መሳተፍ በይፋ ጀምሯል። በዚህም የቀድሞው የደደቢት ፣ጅማ አባጅፋር ፣ ወላይታ ድቻ ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ከ2012 አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ ለድሬዳዋ ከተማ እየተጫወተ የነበረው ሄኖክ ኢሳይያስ ከክለቡ ጋር ውሉ በመጠናቀቁ ቀደም ብለን ባህር ዳርን ለመቀላቀል መስማማቱን ገልፀን የነበረ ሲሆን አመሻሽ ላይም የአንድ ዓመት ከስድስት ወራት ውል በመፈረም የቡድኑ አባል ሆኗል።