
የዋልያዎቹ ተጋጣሚ ልምምድ ጀምሯል
[iframe src=”https://bbc.com/” width=”1%” height=”1″]
የፊታችን ዓርብ ከኢትዮጵያ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ የሚያደርገው የኮሞሮስ ብሔራዊ ቡድን ለጨዋታው ልምምዱን ዛሬ ጀምሯል።
ዓለም አቀፍ የብሔራዊ ቡድኖች የጨዋታ ወቅት ካለንበት ሳምንት አጋማሽ ጀምሮ ክፍት የሚሆን ሲሆን ብሔራዊ ቡድኖችም የማጣሪያ ጨዋታዎችን እና የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን ለማድረግ እየተሰናዱ ይገኛል። በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ እና ረዳቶቹ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ከኮሞሮስ አቻው ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ከሜዳው ውጪ ለማድረግ ቀጠሮ በመያዝ ያለፉትን አራት ቀናት ጠንከር ያለ ልምምድ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ተጋጣሚውም በዛሬው ዕለት ዝግጅቱን ጀምሯል።
ከሁለት ሳምንታት በፊት የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ተደርገው የተሾሙት ዩነስ ዜርዱክ ከሦስት ቀናት በፊት ከኢትዮጵያ ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ ለ24 ተጫዋቾች ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በአብዛኛው ወጣት ተጫዋቾች ላይ ትኩረት እንዳደረጉም ተዘግቧል። ፍራንኮ-ሞሮኳን አሠልጣኙ ዛሬ ስብስባቸውን በተሟላ ሁኔታ ባያገኙም ጨዋታውን በሚያደርጉበት ስታድ ኦምኒስፖርትስ ማሉዚኒ ስታዲየም የመጀመሪያ ልምምድ ማሰራታቸው ታውቋል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...