
ድሬደዋ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን ከከፍተኛ ሊጉ አግኝቷል
አዲስ አሰልጣኝ የሾመው ድሬደዋ ከተማ በከፍተኛ ሊግ ውድድር ጎልተው መውጣት የቻሉ የመሐል ተከላካይ እና አማካይ ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል።
ድሬደዋ ከተማን ለማሰልጠን የተረከቡት አሰልጣኝ ሳምሶም አየለ ከሄኖክ ኢሳያስ ጋር ከመለያየታቸው ውጭ ወደ ዝውውሩ በማግባት ተከላካይ አማረ በቀለን ማስፈረማቸው ይታወቃል። ዛሬ በከፍተኛ ሊጉ የተሳካ ጊዜ ያሳለፉ ሁለት ተጫዋቾችን ከንግድ ባንክ በውሰት አግኝተዋል።
የመሐል ተከላካይ ከድር ሀይረዲን እና አማካይ አባይነህ ፌኖ ለድሬደዋ ከተማ ግማሹን ዓመት ለማገልገል ክለቡ በደብዳቤ ባቀረበው የውሰት ጥያቄ መሰረት ዛሬ ፌዴሬሽን በመገኘት ውላቸውን ያሰፈሩ ሲሆን ረፋድ ላይ ቡድኑን የሚቀላቀሉ ይሆናል።
የመሐል ተከላካይ ከድር ሀይረዲን ከዚህ ቀደም በፋሲል ከነማ በጅማ አባ ጅፋር በሌሎችም ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን ዘንድሮ ንግድ ባንክን በመቀላቀል ቡድኑን በአንበልነት እየመራ ጥሩ ጊዜን ማሳለፍ ችሏል።
አማካይ አባይነህ ፌኖ በወልቂጤ በሀዋሳ ከተማ በሌሎች ክለቦች ግልጋሎት ሲሰጥ ዘንድሮ ወደ ንግድ ባንክን ካመራ በኃላ የተሳካ ጊዜ ካሳለፉ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ሪፖርት | የወራጅ ቀጠናው ተጠባቂ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
ለዓይን ሳቢ የነበረው የአዳማ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ 1-1 መጠናቀቁን ተከትሎ ባህር ዳር ከተማ እና መከላከያ በሊጉ መቆየታቸውን ሲያረጋግጡ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | መከላከያ 1-2 ሀዋሳ ከተማ
ሀዋሳ ከተማ ከመመራት ተነስቶ በማሸነፍ በሦስተኛነት ፉክክሩ ከቀጠለበት ጨዋታ በኋላ ተጋጣሚ አሰልጣኞች ይህንን ብለዋል። አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ - መከላከያ ስለሁለቱ...
ሪፖርት | ሀዋሳ ከተማ መከላከያን አሸንፏል
ሀዋሳ ከተማዎች ደካማ በነበሩበት ጨዋታ አስፈላጊውን ሦስት ነጥብ ከመከላከያ መንጠቅ ችለዋል። መከላከያዎች በመጨረሻው የጨዋታ ሳምንት ከአዳማ ጋር ያለግብ አቻ ከተለያየው...