
ፀሀይነሽ አበበ እና ረዳቶቿ ወደ ብሩንዲ ያቀናሉ
አራት ኢትዮጵያዊያን እንስት ዳኞች የዓለም ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታን ይመራሉ፡፡
በህንድ አዘጋጅነት ለሚካሄደው የዓለም ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ዋንጫ ውድድር ላይ ለመካፈል ኢትዮጵያን ጨምሮ የአፍሪካ ሀገራት በማጣሪያው ጨዋታዎችን እያደረጉ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ በማጣሪያው በቀጣይ ደቡብ አፍሪካን ስትገጥም የመጀመሪያ ዙር ጨዋታቸውን በማሸነፍ ወደ ሁለተኛው ዙር ያለፉት ብሩንዲ እና ታንዛኒያ ደግሞ ቡጁንቡራ ላይ በቀጣዩ ሳምንት ቅዳሜ 10፡00 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ። ይህንንም ጨዋታ አራት ኢትዮጵያዊ ሴት ዳኞች እንዲመሩት ካፍ መመደቡን አውቀናል፡፡
በዚህም ፀሀይነሽ አበበ በመሀል ዳኝነት ጨዋታውን ስትመራው በረዳትነት ደግሞ ወይንሸት አበራ እና ከወሊድ መልስ ወደ ዳኝነት የተመለሰችው ወጋየሁ ዘውዴ እንዲሁም ምስጋና ጥላሁን በአራተኛ ዳኝነት በጨዋታው ተሳትፎ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
*ትናንት ምሽት ምስጋና ጥላሁን ዋና ፀሀይነሽ አበራ ደግሞ አራተኛ ዳኛ መሆናቸውን የጠቆምንበት ዘገባ ላይ ስህተት በመፈፀማችን ባለጉዳዮቹን እና አንባቢዎቻችንን ይቅርታ እንጠይቃለን።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...