
የቀሪ የሊግ ጨዋታዎች የፋሲል ከነማ ዋና አሰልጣኝ ታውቋል
በትናትናው ዕለት ከዋናው አሰልጣኙ ጋር የተለያየው ፋሲል ከነማ በቀጣይ ቡድኑን የሚመሩ አሰልጣኞች ታውቀዋል።
በወቅታዊ ውጤት ማጣት ምክንያት ከአሰልጣኝ ሥዩም ከበደ ጋር ትናንት ማምሻውን በስምምነት ለመለያየት የወሰኑት የፋሲል ከነማ አመራሮች በቀጣይ ቡድኑን እስከ ሰኔ 30 ድረስ በዋና እና በምክትል አሰልጣኝነት የሚመሩትን ግለሰቦች አሳውቀዋል። በዚህም መሠረት ክለቡ ምክትል አሰልጣኝ በመሆን ያለፉትን ሁለት ዓመታት ያገለገሉት ኃይሉ ነጋሽ (ቲጋና) ወደ ዋና አሰልጣኝነት ከፍ አድርጎ ሲሾም እንዲሁ በሁለተኛ ምክትልነት ኃላፊነት የነበራቸው ሙልቀን አቡሃይን በዛው የሥራ ድርሻቸው እንዲቀጥሉ ወስኗል።
ዘለግ ላለ ሰዓት በትናትናው ምሽት ከተጫዋቾቹ ጋር ስብሰባ የተቀመጠው የክለቡ ቦርድ አሉ በሚባሉ ክፍተቶች ዙርያ ሰፊ ውይይት ማድረጉ ሲታወቅ ሌሎች ውሳኔዎችን በቀጣይ ይወስናል ተብሎ ይጠበቃል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአሰልጣኞች አስተያየት | ፋሲል ከነማ 1-0 ሀዋሳ ከተማ
ፋሲል ከነማዎች ወሳኝ ድል ካስመዘገቡበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሽ - ፋሲል ከነማ...
ሪፖርት | ዐፄዎቹ ከመሪው ያላቸው የነጥብ ልዩነት ወደ አንድ ቀንሰዋል
እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የፋሲል ከነማ እና የሀዋሳ ከተማ ጨዋታ ፋሲሎች በመጂብ ቃሲም ብቸኛ ግብ በድል መወጣታቸውን ተከትሎ ከቅዱስ ጊዮርጊስ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ28ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች
የጨዋታ ሳምንቱ የመጨረሻ ቀን ሦስት መርሐ-ግብሮች ላይ የሚያጠነጥነው ዳሰሳችን እንደሚከተለው ተሰናድቷል። አርባምንጭ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና ካለፉት አምስት ጨዋታዎች አንዱንም...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...