
የሁለተኛ ዙር የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሚጀመርበት ጊዜ እና ቦታ ታውቋል
በ13 ክለቦች መካከል እየተከናወነ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛ ዙር ውድድር የሚጀምርበት ቀን እና ቦታን ፌዴሬሽኑ ይፋ አድርጓል።
በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥር የሚከናወነው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ዘንድሮ ጅማሮውን በሀዋሳ አድርጎ በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር ከተማ እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል። በቀጣዩ ሳምንት የመጀመሪያ ቀናትም የመጀመሪያውን ዙር ውድድር የሚያገባድድ ይሆናል። የሊጉ የበላይ አካል የሆነው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሁን እንዳስታወቀው ከሆነ ደግሞ የሁለተኛው ዙር ውድድር ከግንቦት 14 ጀምሮ በአዳማ ከተማ ይከናወናል።
ለክለቦቹ በተላከው ደብዳቤ መሠረት የመጀመሪያው ዙር ውድድር ሚያዚያ 25 ከተከባደደ በኋላ ከሚያዚያ 29 ጀምሮ እስከ ግንቦት 12 ድረስ የውድድር አጋማሽ የዝውውር መስኮት ክፍት እንደሚሆን ተጠቁሟል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ወሳኝ ድል አሳክተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በተደረጉ አራት መርሐግብሮች ጅምሩን ሲያደርግ መከላከያ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ተጋጣሚዎቻቸውን...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 1-1 ድሬዳዋ ከተማ
በሊጉ ለመቆየት ብርቱ ትግል ተደርጎበት ነጥብ በመጋራት ከተጠናቀቀው ጨዋታ ፍፃሜ በኋላ አሰልጣኞች የድህረ-ጨዋታ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ - አዳማ...
ከ17 እና ከ15 ዓመት በታች ውድድሮች የሚደረጉበት ቦታ እና ቀን ይፋ ሆኗል
የ2014 ከ17 ዓመት በታች እና ከ15 ዓመት በታች የፓይለት ፕሮጀክት ውድድሮች የሚደረጉበት ከተማ እና ቀን ታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌድሬሽን...
የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ዝርፊያ ተፈፀመባቸው
በሲዳማ ቡና ሽንፈት ያስተናገድው የአዲስ አበባ ከተማ የቡድን አባላት ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ሶከር ኢትዮጵያ አውቃለች። ረፋድ ላይ በ29ኛ...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...