
በሊጉ አዲስ የዳኝነት አተገባበር ነገ ይጀምራል
በነገው ዕለት በባህር ዳር በሚጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አዲስ የዳኝነት ሚና መተግበር እንደሚጀምር ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 የአራተኛ ከተማ ውድድሩን ከነገ ጀምሮ በባህር ዳር ከተማ ማከናወን ይጀምራል። ከዚህ ቀደም በነበሩት ሦስት ከተሞች ውድድር ላይ መጠነኛ የዳኝነት እፀፆች ሲስተዋሉ የነበረ ሲሆን በተለይ ደግሞ ጎል ጋር ከመስመር ያለፉ እና ያላለፉ ኳሶች ጉዳይ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበር አይዘነጋም። የተሻለ የቴክኖሎጂ ድጋፍ የሌለውን የሀገራችን ዳኝነት ውሳኔዎች ለማሳደግ ደግሞ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ የዳኝነት ሚና መተግበር እንደሚጀምር ይፋ ሆኗል።
በአሁኑ ሰዓት በባህር ዳር አዝዋ ሆቴል የውድድሩ የበላይ አካል ከክለብ ተወካዮች ጋር እያደረገ በሚገኘው ስብሰባ ላይ የተገኙት የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ተወካይ እና የጨዋታ ኮሚሽነር የሆኑት አቶ አዲሱ ነጋሽ ከነገ ጀምሮ ስድስት ዳኞች በጨዋታዎች እንደሚመደቡ ተናግረዋል። ከዋና እና ሁለት የመስመር እንዲሁም አንድ አራተኛ ዳኛ ውጪ የሚጨመሩት ሁለት የጎል አጠገብ ዳኞች እንደሆኑ ተገልጿል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች ከመቋረጡ አስቀድሞ የሚደረጉትን የነገ ጨዋታዎች እንደሚከተለው ዳሰናል። ባህር ዳር ከተማ ከ ሲዳማ ቡና የነገው የጨዋታ ቀን...
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
ሪፖርት | ፋሲል ከነማ የቅዱስ ጊዮርጊስን ያለመሸነፍ ጉዞ ገቷል
እጅግ ተጠባቂ በነበረው የዕለቱ የመጨረሻ ጨዋታ ፋሲል ከነማ በኦኪኪ አፎላቢ ጎል ቅዱስ ጊዮርጊስን 1-0 በማሸነፍ የነጥብ ልዩነቱን ወደ አምስት ቀንሷል።...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 3-0 ሰበታ ከተማ
ለሰባ አራት ደቂቃዎች በጎዶሎ ተጫዋቾች የተጫወተው አዳማ ከተማ ሶስት ነጥብ ካገኘበት ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ አሰልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ...