
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የምድብ ድልድል ወጥቷል
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት በሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ውድድር ላይ ኢትዮጵያ የምድብ ተጋጣሚዎቿን አውቃለች።
በምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ (ሴካፋ) አስተናጋጅነት ለሚከወነው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የምድብ ድልድል ዛሬ ይፋ ሆኗል፡፡ ከግንቦት 14 ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት ቀናት ይደረጋል በተባለው (የሚጀመርበት ቀን ሊለወጥ ይችላል) እና በዩጋንዳ አስተናጋጅነት በሚከናወነው ውድድር ላይ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በድምሩ ስምንት ሀገራት ተካፋይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በዚህም መሰረት ውድድሩ በሁለት ምድቦች ተከፍሎ የሚደረግ ሲሆን የምድብ ድልድሉ የሚከተለው ሆኗል:-
በምድብ 1 ዩጋንዳ ፣ ብሩንዲ ፣ ሩዋንዳ ፣ ጅቡቲ
በምድብ 2 ኢትዮጵያ ፣ ታንዛኒያ ፣ ዛንዚባር እና ደቡብ ሱዳን
በተያያዘ ዜና በያዝነው ወር ግንቦት 16 በአዳማ ከተማ ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር በዚህ የሴካፋ ዋንጫ ውድድር የተነሳ ሊራዘም የሚችልበት ዕድል የሰፋ መሆኑን ሰምተናል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውሎ
የ2014 የአንደኛ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው አዲስ ከተማ፣ ሮቤ ፣ ዱራሜ እና ጂንካ ወደ ከፍተኛ ሊግ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...