
ኢትዮጵያ ግብፅን የምትገጥምበት ስታዲየም ታውቋል
የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም በካፍ ተቀባይነት አለማግኘቱን ተከትሎ ዋሊያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያቸውን ሁለተኛ ጨዋታ የሚያደርጉበት ስታዲየም ታውቋል።
ከቀናት በፊት በእገዳ ላይ የቆየው የባህር ዳር ዓለምአቀፍ ስታዲየም በካፍ ባለሙያ ተገምግሞ አህጉራዊ ውድድሮችን ለማስተናገድ አሁንም ብቁ አለመሆኑ መገለፁ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሜዳ ጨዋታዎቿን የት ልታደርግ እንደምትችል ሲጠበቅ ነበር።
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ምሽቱን በድረገፁ ባስታወቀው መሰረትም የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ባደረገው ስብስባ ዋልያዎቹ በሜዳቸው ያደርጉት የነበረውን የምድቡን ሁለተኛ ጨዋታ ከግብፅ ጋር በማላዊ ዋና ከተማ ሊሎንግዌ በሚገኘው እና አሁን ላይ በካፍ በፀደቀው ቢንጉ ስታዲየም እንዲያደርጉ ውሳኔ አሳልፏል። ፌዴሬሽኑ እንዳለው ይህ ውሳኔ በማላዊ መንግሥት እና እግርኳስ ፌዴሬሽን ይሁንታን ያገኘ ሲሆን ካፍም በሀሳቡ እንደተስማማ የሚገልፅ ደብዳቤ ልኳል።
በመሆኑም ዋሊያዎቹ ማጣሪያውን ሲጀምሩ ግንቦት 25 ላይ ከማላዊ ብሔራዊ ቡድን የሜዳ ውጪ ጨዋታቸውን ከካደረጉ በኋላ እዛው ቆይተው ከአራት ቀናት በኋላ ከፈርኦኖቹ ጋር እንደሚፋለሙ ይጠበቃል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል
የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል። በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ...
በወርሀዊ የፊፋ የሀገራት ደረጃ ዋልያው ሁለት ደረጃዎችን ቀንሷል
ከደቂቃዎች በፊት ይፋ በሆነው የፊፋ የሀገራት ደረጃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ደረጃዎችን ሸርተት ብሏል። የዓለም እግር ኳስ የበላይ አካል የሆነው...
ዋልያው ከሜዳው ውጪ ጥሩ በተንቀሳቀሰበት የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ተረቷል
[iframe src="https://bbc.com/" width="1%" height="1"] ከኮሞሮስ አቻው ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 2-1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል። ጨዋታውን ለመጀመር...
ከነገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ በፊት የኮሞሮስ ተጫዋቾች ሀሳብ ሰጥተዋል
[iframe src="https://bbc.com/" width="1%" height="1"] 👉"ለቀልድ ስላልሆነ የተሰባሰብነው ጨዋታውን በትኩረት እንቀርባለን" መሐመድ የሱፍ 👉"የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫው ያደረጋቸውን ጨዋታዎች ተከታትለናል"...
ስድስት ተጫዋቾች ከዋልያዎቹ ስብስብ ተቀንሰዋል
ከኮሞሮስ ጋር ለሚደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ለ30 ተጫዋቾች ጥሪ ያቀረበው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስድስት ተጫዋቾችን መቀነሱ ታውቋል። በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ...
የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋቾች ብሔራዊ ቡድኑን አልተቀላቀሉም
[iframe src="https://bbc.com/" width="1%" height="1"] መጋቢት 16 ከኮሞሮስ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ለማድረግ በትናንትናው ዕለት የተሰባሰበው ዋልያው ከኢትዮጵያ ቡና የጠራቸውን 5 ተጫዋቾች...