
ሲዳማ ቡና አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌን ለማሰናበት ወስኗል
ከደቂቃዎች በፊት የሲዳማ ቡና አመራሮች ባደረጉት ውይይት አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ከክለቡ እንዲሰናበቱ መወሰናቸው ተረጋግጧል።
በ2013 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የአሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉን መለያየት ተከትሎ ነበር የቀድሞው የመከላከያ ፣ ደደቢት ፣ ጅማ አባ ጅፋር እና መቐለ 70 እንደርታ አሰልጣኝ የነበሩት ገብረመድህን ኃይሌ ሲዳማ ቡናን በመረከብ ቡድኑን ከመውረድ ስጋት አትርፈውት የነበረው፡፡
የአምናውን ውጤት ተከትሎ ክለቡ ከአሰልጣኙ ጋር ለሁለት ዓመታት አብሮ ለመዝለቅ ወስኖ ነበር። ሆኖም የአሰልጣኙ የእስካሁኑ ጉዞ ክለቡ ባስቀመጠው ቅድመ መመሪያ መሠረት እየሄደ አይደለም በሚል ዛሬ በመከላከያ 5-3 መሸነፋቸውን ተከትሎ የክለቡ አመራሮች ባደረጉት ውይይት አሰልጣኙ ከኃላፊነት እንዲነሱ ወስነው ወጥተዋል፡፡
ክለቡ አመሻሽ ላይ ለአሰልጣኙ የመልቀቂያ ደብዳቤ የሚሰጡ መሆኑን የሰማን ሲሆን አሰልጣኝ ገብረመድህንም ክለቡ በባህር ዳር ባረፈበት ሆቴል እንደማይገኙ ተሰምቷል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአሰልጣኞች አስተያየት | አርባምንጭ ከተማ 0-0 ወላይታ ድቻ
ያለጎል ከተጠናቀቀው ጨዋታ በኃላ አሰልጣኞች ተከታዩን አስተያየት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ- አርባምንጭ ከተማ ስለጨዋታው “የመጀመርያው አጋማሽ በተቻለ መልኩ ለማጥቃት ጥረት...
ሪፖርት | ፉክክር አልባው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል
የግብ ሙከራዎች ባልነበሩበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል። አርባምንጭ ከተማዎች ሀዋሳን ከረታው ስብስብ ባደረጓቸው ሁለት...
ሪፖርት | አዳማ ከ11 ጨዋታ በኋላ አሸንፏል
በረፋዱ ጨዋታ ለ73 ያክል ደቂቃዎች በጎዶሎ የተጫዋች ቁጥር ያሳለፉት አዳማ ከተማዎች በውድድር ዘመኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሦስት ግቦችን ባስቆጠሩበት ጨዋታ ከ11...
የ2014 የሴቶች ከፍተኛ ሊግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ አሸናፊነት ተጠናቋል
በአስራ አራት ክለቦች መካከል ከታህሳስ 16 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለት ክለቦችን ወደ ፕሪምየር ሊጉ በማሳደግ ተጠናቋል፡፡ በኢትዮጵያ...
ቅድመ ዳሰሳ | ፋሲል ከነማ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሁለተኛ ቦታ ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ፋሲል ከነማ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ እንደሚከተለው ቃኝተነዋል። የወቅቱ...
ቅድመ ዳሰሳ | የ25ኛ ሳምንት የመጀመሪያ ቀን ጨዋታዎች
ሊጉ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት እና ጨዋታዎች ከመቋረጡ በፊት የሚደረጉት የጨዋታ ሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ፍልሚያዎች እንዲህ ተዳሰዋል። አዲስ አበባ ከተማ ከ...