
አዳማ ከተማ ከአሠልጣኙ ጋር ተለያይቷል
ያለፉትን አስር ጨዋታዎች በሊጉ ማሸነፍ ያልቻለው አዳማ ከተማ ከአሠልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር በስምምነት መለያየቱን ሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጣለች።
የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከመጀመሩ በፊት አዳማ ከተማን ለማሠልጠን ፊርማውን ያኖረው አሠልጣኝ ፋሲል ተካልኝ በዝውውር መስኮቱ ራሱን በማጠናከር ውድድር ቢጀምርም እስካሁን ከአራት ጨዋታዎች በላይ ቡድኑን ለድል ማብቃት አልቻለም። በእንቅስቃሴ ደረጃ ብዙ የሚያስተቹ ችግሮች ቡድን ላይ ባይኖሩም ጨዋታን ከማሸነፍ ጋር ተያይዞ ባለ ክፍተት የክለቡ አመራር ከደቂቃዎች በፊት አሠልጣኙ ላይ ውሳኔ ማሳለፉን አውቀናል።
ከትናንቱ የባህር ዳር ከተማ ሽንፈት ማግስት ከአሠልጣኝ ፋሲል ተካልኝ ጋር ለመነጋገር የተቀመጠው የክለቡ አመራርም በስምምነት እንዲለያዩ ማድረጉን አውቀናል። በቀሪ የሊጉ ጨዋታዎች ቡድኑን በጊዜያዊነት እያሰለጠነ እንዲቀጥል ደግሞ የፋሲል ምክትል የነበረው ይታገሱ እንዳለ ተመርጧል። ሁለተኛው ምክትል አሠልጣኝ አብዲ ቡሊ ደግሞ ይታገሱን እንዲረዳ መደረጉን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
አዳማ ቀጣይ የሊጉ መርሐ-ግብሩን በሳምንቱ መጨረሻ በደረጃ ሰንጠረዥ ግርጌ ከሚገኘው ሰበታ ከተማ የሚያደርግ ይሆናል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
ቅድመ ዳሰሳ | የ29ኛ ሳምንት ሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች
የነገውን ተጠባቂ የጨዋታ ቀን የተመለከተው ዳሰሳችን እንዲህ ይነበባል። ወደ ፍፃሜው እየቀረበ በሚገኘው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ነገ እጅግ አጓጊ የሆነ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ባህርዳር ከተማ 1-1 ሰበታ ከተማ
የዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ክለብ አሰልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ - ባህርዳር ከተማ ስለ ሁለቱ...
ሪፖርት | በሁለቱ አጋማሾች የተቆጠሩት ድንቅ ጎሎች ባህር ዳር እና ሰበታን ነጥብ አጋርተዋል
በዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ እና ሰበታ ከተማ በውብ ግቦቻቸው አንድ እኩል ወጥተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ድሬዳዋ ከተማን አንድ ለምንም...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ሀዲያ ሆሳዕና 2-2 ወላይታ ድቻ
ከጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር በኋላ ሁለት አቻ ከተጠናቀቀው ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት...
ሪፖርት | ወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ነጥብ ተጋርተዋል
ጥሩ ፉክክር ያስተናገደው የምሳ ሰዓቱ የወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ 2-2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከቅዱስ ጊዮርጊሱ ጨዋታ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ወልቂጤ ከተማ 3-0 ጅማ አባ ጅፋር
ከረፋዱ ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ለሱፐር ስፖርት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ተመስገን ዳና - ወልቂጤ ከተማ ስለጨዋታው "መውረዱን...