
በሦስት ዳኞች ላይ ውሳኔ ተላልፏል
በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ ዳኞች ከፕሪምየር ሊጉ ውድድር ተሸኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና በሀድያ ሆሳዕና 1-0 መረታቱ ይታወሳል፡፡ ይህን ጨዋታ በዋና ዳኝነት የመሩት ፌዴራል ዳኛ ሚካኤል ጣዕመ በተጫዋቾች ላይ አላስፈላጊ ቃላትን ስለመጠቀማቸው ሪፖርት የቀረበባቸው ሲሆን ኢትዮጵያ ቡናም የቴክኒክ ክስ አስይዞ ነበር፡፡ ጉዳዩን የተመለከተው የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ዳኛው ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ከፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች እንዲሸኙ ማድረጉን የሊጉ አክሲዮን ማህበር ይፋ አድርጓል፡፡
አነጋጋሪ በነበረው በሳምንቱ የማሳረጊያ ጨዋታ ወላይታ ድቻ እና ሲዳማ ቡና የተገናኙበት ጨዋታ በሲዳማ አሸናፊነት ሲጠናቀቅ ተበድያለሁ ያለው ወላይታ ድቻ ለአክስዩን ማህበሩ አቤቱታውን አቅርቧል። ክለቡ ባቀረባቸው ሁለት ክሶች ያልተገባ የፍፁም ቅጣት ምት እንደተሰጠበት እንዲሁም ያገኘውን ፍፁም ቅጣት ምት ደግሞ የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ መስመሩን ለቆ እንዳዳነበት በመግለፅ የዕለቱን ዳኞች ተጠያቂ አድርጎ ነበር። የሊጉ አክሲዮን ማህበር ይፋ እንዳደረገው ክሱን የተመለከተው የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ጨዋታውን መርተው የነበሩት ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ለሚ ንጉሴ እና ረዳት ሳኛ አብዱ ይጥና የዚህን ዓመት ቀጣይ ጨዋታዎች እንዳይመሩ በሚል ከውድድሩ አሰናብቷል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የአሰልጣኞች አስተያየት | ባህርዳር ከተማ 1-1 ሰበታ ከተማ
የዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም ክለብ አሰልጣኞች አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ - ባህርዳር ከተማ ስለ ሁለቱ...
ሪፖርት | በሁለቱ አጋማሾች የተቆጠሩት ድንቅ ጎሎች ባህር ዳር እና ሰበታን ነጥብ አጋርተዋል
በዕለቱ ሦስተኛ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ እና ሰበታ ከተማ በውብ ግቦቻቸው አንድ እኩል ወጥተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ድሬዳዋ ከተማን አንድ ለምንም...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ሀዲያ ሆሳዕና 2-2 ወላይታ ድቻ
ከጥሩ የሜዳ ላይ ፉክክር በኋላ ሁለት አቻ ከተጠናቀቀው ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት...
ሪፖርት | ወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ነጥብ ተጋርተዋል
ጥሩ ፉክክር ያስተናገደው የምሳ ሰዓቱ የወላይታ ድቻ እና ሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታ 2-2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀዲያ ሆሳዕና ከቅዱስ ጊዮርጊሱ ጨዋታ...
የአሰልጣኞች አስተያየት | ወልቂጤ ከተማ 3-0 ጅማ አባ ጅፋር
ከረፋዱ ጨዋታ መጠናቀቅ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች አሰልጣኞች ተከታዩን ሀሳብ ለሱፐር ስፖርት ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ተመስገን ዳና - ወልቂጤ ከተማ ስለጨዋታው "መውረዱን...
ሪፖርት | ወልቂጤ የሊጉ ቆይታውን ለማረጋገጥ ተቃርቧል
በ29ኛ የጨዋታ ሳምንት የመክፈቻ በነበረው መርሐ-ግብር አምበሉ ጌታነህ ከበደን መልሰው ያገኙት ወልቂጤ ከተማዎች ጅማ አባ ጅፋርን በመርታት ደረጃቸውን አሻሽለዋል። ወልቂጤ...