ብሔራዊ ቡድኑ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርቧል

የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከቀናት በኋላ ማድረግ የሚጀምረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫዋቾቹ ጥሪ አስተላልፏል።

በ2023 በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የሚበቁ ብሔራዊ ቡድኖችን ለመለየት የማጣሪያ ጨዋታዎች በቅርቡ መደረግ የሚጀምሩ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም የምድብ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ጨዋታውን ከማላዊ እና ግብፅ ጋር የሚያደርግ ይሆናል። ለሁለቱ ወሳኝ ጨዋታዎች ደግሞ የቡድኑ ዋና አሠልጣኝ ውበቱ አባተ ለ28 ተጫዋቾች ጥሪ ማቅረባቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ይፋ አድርጓል።

ጥሪ የቀረበላቸው ተጫዋቾች የሚከተሉት ናቸው

ግብ ጠባቂዎች

ፋሲል ገብረሚካኤል (ባህር ዳር ከተማ)
በረከት አማረ (ኢትዮጵያ ቡና)
ዳግም ተፈራ (ሀዋሰ ኣከተማ)
ሰዒድ ሀብታሙ (ወልቂጤ ከተማ)

ተከላካዮች

አስራት ቱንጆ (ኢትዮጵያ ቡና)
ረመዳን የሱፍ (ወልቂጤ ከተማ)
ሄኖክ አዱኛ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
ሱሌይማን ሀሚድ (ቅዱእ ጊዮርጊስ)
ብርሀኑ በቀለ (ሀዲያ ሆሳዕና)
ምኞት ደበበ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
ያሬድ ባዬ (ፋሲል ከነማ)
ጊት ጋትኩት (ሲዳማ ቡና)
ሚሊዮን ሰለሞን (አዳማ ከተማ)

አማካዮች

አማኑኤል ዮሐንስ (ኢትዮጵያ ቡና)
ጋቶች ፓኖም (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
ሱራፌል ዳኛቸው (ፋሲል ከነማ)
በዛብህ መለዮ (ፋሲል ከነማ)
መስዑድ መሐመድ (ጅማ አባ ጅፋር)
ቢኒያም በላይ (መከላከያ)
ወንድማገኝ ኃይሉ (ሀዋሳ ከተማ)
ሽመልስ በቀለ (ኤል ጎውና/ግብፅ)

አጥቂዎች

አማኑኤል ገብረሚካኤል (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
ቸርነት ጉግሳ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)
ዳዋ ሆቴሳ (አዳማ ከተማ)
በረከት ደስታ (ፋሲል ከነማ)
አቡበከር ናስር (ኢትዮጵያ ቡና)
ይገዙ ቦጋለ (ሲዳማ ቡና)
ሀብታሙ ታደሰ (ሀዲያ ሆሳዕና)