
ሱራፌል ዳኛቸው ለነገው ጨዋታ ይደርስ ይሆን ?
ነገ ምሽት የግብፅ ብሔራዊ ቡድንን የሚገጥመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አማካዩን ሊያጣ ይችላል።
የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታዎች በአህጉራችን የተለያዩ ሀገራት እየተከናወኑ የሚገኝ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም በነገው ዕለት በቢንጉ ስታዲየም የግብፅ አቻውን ይፋለማል። ለጨዋታው በጥሩ ሞራል እየተዘጋጀ የሚገኘው ብሔራዊ ቡድኑ አማካዩ ሱራፌል ዳኛቸው ከጨዋታው ውጪ እንደሆነ ተመላክቷል።
ገና የብሔራዊ ቡድን ጥሪው ሲደርሰው መጠነኛ ጉዳት የነበረበት ሱራፌል ራሱን እየጠበቀ ልምምድ እየሰራ ቆይቶ እሁድ በተደረገው የማላዊ ጨዋታ ላይ ቢሳተፍም ጉዳቱ አገርሽቶበት ዕረፍት ሰዓት ላይ ተቀይሮ እንደወጣ ይታወቃል። ጭኑ ላይ የመቀጥቀጥ ጉዳት ያስተናገደው ተጫዋቹ ከጨዋታው ማግስት በነበሩት ሁለት የልምምድ መርሐ-ግብሮች ላይም መሳተፍ ሳይችል ቀርቷል። ቡድኑ ዛሬ አመሻሽ ከጨዋታው በፊት በሚሰራው የመጨረሻ ልምምድ የሚቀየሩ ነገሮች ከሌሉ በስተቀር ተጫዋቹ አሁን ባለበት ሁኔታ ለጨዋታው ብቁ ስለማያደርገው እንደማይጫወት ተጠቁሟል።
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | የሊጉ መሪ ንግድ ባንክ እና ተከታዩ ኤሌክትሪክ ሲያሸንፉ ሀዋሳ እና መከላከያ ነጥብ ተጋርተዋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 16ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ በአዳማ ሲከወኑ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ንግድ ባንክ በግብ ሲንበሸበሽ ተከታዩ ኢትዮ ኤሌክትሪክ...
አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ቅጣት ተላለፈባቸው
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 28ኛ ሳምንትን ተከትሎ የተለያዩ የዲሲፕሊን ውሳኔዎች ተወስነዋል። ሊጠናቀቅ የሁለት ሳምንት ዕድሜ የቀረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ...
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን ሸኝቷል
ከወረጅ ቀጠናው ለመውጣት እየጣረ የሚገኘው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾቹን በዲሲፕሊን ምክንያት ከስብስቡ መቀነሱ ታውቋል። በ28ኛ ሳምንት ከመከላከያ ጋር ያለ ጎል...
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ | ተጠባቂው ጨዋታ ነጥብ በመጋራት ተጠናቋል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት ስድስት ጨዋታዎች ዛሬ በሁለት ስታዲየሞች ሲደረጉ ተጠባቂው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታ...
ድሬዳዋ ከተማ የዛሬውን ጨዋታ መነሻ በማድረግ ቅሬታውን አቅርቧል
በ28ኛው ሳምንት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ቀትር ላይ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ለሊጉ የበላይ አካል የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቷል። በባህር ዳር ስታዲየም...
ሪፖርት | ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ነጥብ ተጋርተዋል
በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያይተዋል። ባሳለፍነው ሳምንት በሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ለምንም የተረቱት...